• በቅርብ የተጻፉ

    Tuesday 10 November 2015

    የመገለጥ ሃይማኖት በአስተርእዮ


    በዲያቆን ብርሃኑ አድማስ

    ሃይማኖት የምንቀበለውናየምንጠብቀው እንጂየምንሠራውና የምናሻሽለው አይደለም ከታኅሣሥ29 ቀን ጀምሮ እስከ ዐቢይ ጾም መግቢያ ድረስያለው ወቅት /ጊዜ/ ዘመነ አስተርእዮ /የመገለጥወራት/ እየተባለ ይጠራል፡፡ በታኅሣሥ 29 ቀንየጌታችን ልደት ስለሆነ በዚህ አምላክ በሥጋየተገለጠበት በዓል ይከበራል፡፡ ጥር 11 ቀን ደግሞበጌታችን ጥምቀት የሥላሴ አንድነት ሦስትነትበይፋ የተገለጠበት ነው፡፡ ጥር 12 ቀን ደግሞጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህምድር ማስተማር በጀመረበት ጊዜ በቃና ዘገሊላሰርግ ቤት ተገኝቶ ውኃውን ወደ ወይን በመለወጥአምላክነቱን በይፋ የገለጠበት በዓል ነው፡፡ እነዚህሦስት ዓበይት መገለጦች ወቅቱን በአጠቃላይእግዚአብሔር ለሰው ልጅ የተገለጠበትንመታሰቢያአደረጉት፡፡ አምልኮተ እግዚአብሔርንትክክለኛሃይማኖት ከሚያሰኙት መሠረታዊ ነጥቦች ዋነኛውናቀዳሚው የመገለጥ ሃይማኖት/Revealed Religion/ መሆኑ ነው፡፡

    የአምላክን ማንነት በእምነት ለሚመረምር ሰውአምላክ ያልተፈጠረና ሁሉን የፈጠረ፣ የማይወሰን፣በጊዜም የማይለካ ማለት ከጊዜና ቦታ ውጭ /Out of space time/ መሆኑ ሊጠረጠር አይችልም፡፡ስለዚህ አምላክ ከቦታና ጊዜ ውጭ ከሆነና በሁሉምቦታ ደግሞ የመላ ወይም ምሉዕ ከሆነ/Omni present/ በቦታ ጊዜ ውስጥ ያሉ ፍጥረታትአምላክን ሊያዩት አይቻላቸውም ማለት ነው፡፡ ይህንሃሳብ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረትነትእናብራራው፡፡«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙዓይነትና በብዙ ጐዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም «ዘመናትን»በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛተናገረን» /ዕብ 1፥1/ በሚለው የቅዱስ ጳውሎስትምህርት ውስጥ «ዘመን» ወይም ጊዜ ፍጥረትመሆኑን በግልጽ እንረዳለን፡፡

    መፍቀሬ ጥበብ ሰሎሞንም «ጥበብ ቤቷን ሠራች፤ሰባት ምሰሶዎችንም አቆመች» /ምሳ 9፥1/በማለት በምሳሌው ተጨማሪ ምስክርነት ሰጥቷል፡፡ሊቃውንት በትርጓሜ እንዳብራሩት«ጥበብ» የተባለጌታ «ቤት» የተባለ ዓለምን ፈጥሮአል፡፡ ዓለሙየጸናባቸው «ሰባት ምሰሶዎች» ደግሞ ዓለምንእስከ ዕለተ ምጽአት የሚያጸኑት አዕዋዳት ሰባቱዕለታት ናቸው፡፡ በሌላ አነጋገር ዓለምን የአጸናውጊዜ ነው ማለት ነው፡፡ሙሴ «በመጀመሪያእግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ» ዘፍ 1፥1ባለበት የሥነ ፍጥረት መጽሐፍም ጨለማ የነበረመሆኑን ከተረከልን በኋላ « ብርሃን ይሁን አለ»ይልና ጠዋትም ሆነ ማታም ሆነ አንድ ቀን በማለትዓለምና ጊዜ አንድ ላይ መፈጠራቸውን ይነግረናል፡፡ከዚያም አስከትሎ የቀሪዎቹን የአምስት ቀንፍጥረታትና የመጨረሻዋን/የሰባተኛውን/ ዕለትዕረፍትነት ነግሮን ያጠቃልላል፡፡ከዚያ በኋላ ዓለምይቀጥላል፤ የዕለታቱ ዑደትም ይቀጥላል፡፡ በሰባትዕለት አጸናው ማለት ይህ ነው፡፡ ሁሉንም እርሱእንደፈጠረ ደግሞ « ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውምአንዳች እንኳ ያለ እርሱ የሆነ የለም፤» ዮሐ 1፥3

     «የሚታዩትና የማይታዩት ዙፋናት ቢሆኑ ወይምጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናትበሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱተፈጥረዋልና፤ከፍጥረት ሁሉ በፊት በእርሱ ነው፤ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል፤ እርሱም ከሁሉበፊት ነው፤ ሁሉም በእርሱ ተጋጥሞአል» /ቆላ.1፥15-17/ ተብሎ ስለተጻፈ አምላክ በቅዱሳትመጻሕፍትም ከቦታ ጊዜ ውጭ መሆኑ የተረጋገጠነው፡፡ፈጣሪ ከቦታ ጊዜ ውጭ ከሆነ ሊያየውየሚቻለው ፍጥረት የለም ማለት ነው፡፡ ወንጌላዊዮሐንስ «መቼም ቢሆን እግዚአብሔርንያየው አንድስንኳ የለም» /ዮሐ 1፥18/ እንዳለ፡፡በመቃብያንም«አንተን ሁሉን ታያለህ እንጂ አንተንማየት የሚችል የለም» ተብሎ ተጽፎአል፡፡3ኛመቃ.9፥26 ቅዱስ ጳውሎስም «ማንም ሊቀርበውበማይችል ብርሃን ይኖራል፤ አንድ ሰው እንኳአላየውም፤ ሊያየውም አይቻለውም» /1ኛጢሞ.6፥16/ ሲል እንዳጸናው ለፍጥረትእግዚአብሔርንማየት አይቻልም፡፡ ይህም ብቻአይደለም፤ እርሱን በምርምር ማወቅም አይቻልም፡፡አካሉ ረቂቅና ምሉዕ፣ በቦታ ጊዜ የማይወሰን ከሆነማን በምን ሊመረምረው ይችላል፡፡ በግብሩበባሕርዩ እንመርምረው እንዳንል በእኛ ኅሊናችንኅሊናን የፈጠረውን መመርመር ሸክላ ሠሪውንለማወቅ ከመጣር የበለጠ የማይቻል ነው፡፡

    ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት «ወረሰየ ጽልመተምስዋሮ፤ ጨለማን መሰወሪያው አደረገ» እንዳለውሊመረመር አይችልም፡፡ በጨለማ ማየትእንደማይቻል ሁሉ የእግዚአብሔርባሕርይሊመረመር የማይቻል ነውና፡፡ ታዲያ ፈጣሪን እንዴትማወቅ ይቻላል? የሚለው ጥያቄ በዚህ ጊዜ ሊነሳየሚገባ ነው፡፡ መልሱም ቀላል ነው፡፡ የምናውቀውእርሱ ራሱ ሲገለጥልንና ሲገልጥልን ብቻ ነው፡፡ከተገለጠበትናከገለጠውም መጠን በላይ ማወቅአይቻልም፡፡ ስለዚህ የእውነተኛ ሃይማኖትነትመሠረታዊ ማረጋገጫዎች መካከል አንዱና ዋናውመገለጥ ነው ያልነው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ራሱንባይገልጥ ማን በምን መንገድ ሊያውቀው ይችላል፡፡አምልኮተ እግዚአብሔርንበሦስቱም ሕግጋት /በሕገ ልቡና፣ በሕገ ኦሪት፣ በሕገ ወንጌል/ብንመረምረው መንገዱ ሁሉ መገለጥ ብቻ ሆኖእናገኘዋለን፡፡

    እግዚአብሔር ራሱን ለመላእክት በመፍጠርገለጠላቸው፡፡ለአዳም ተገለጠለት፣ አነጋገረው፣ትእዛዝም ሰጠው፡፡ ከበደለውም በኋላ ፈለገው፤አነጋገረው፤... የሚሉት በሙሉ መገለጥንየሚያመላክቱ ናቸው፡፡ ለምሳሌ በኦሪት ዘፍጥረትላይ እግዚአብሔር አዳምን «አዳም አዳም ወዴትነህ?» አለው የሚለው ያለበትን ያለማወቅ ሳይሆንአዳም ከበደለም በኋላ ለኃጢአተኛ ባሕርዩበሚስማማ ሁኔታ መገለጡን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ከዚህም በኋላ በሕገ ልቡና ለአባቶች ሁሉበየዘመናቸው እንደ ሃይማኖታቸው ጽናት እንደአእምሮአቸው ስፋት ሲገለጥላቸው ኖርአል፡፡«በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለእግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት»ተብሎ ስለ አብርሃም የተጻፈው ነው፤ /ዘፍ. 18፥1/የሚለው የዚህ ማረጋገጫ ነው፡፡ይሁን እንጂእግዚአብሔር በየዘመኑ ለነበሩ ሰዎች የተገለጠበትመንገድ የተለያየ ከጥንት ወደ አሁን ጊዜስንመለከተውምየበለጠ እየተገለጠ እንደመጣቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ ለምሳሌ የሕገ ኦሪትመሥራች ለምንለው ለሙሴ ሲገለጥለትለአብርሃም ከገለጠለት በላይ ለእርሱእንደገለጸለትነግሮታል፡፡ «እግዚአብሔርም ሙሴንተናገረው፣ አለውም እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ለአብርሃምም፣ለይስሐቅም፣ ለያዕቆብም ሁሉንእንደሚችል አምላክ ተገለጥሁ፣ ነገር ግን ስሜእግዚአብሔር አልታወቀላቸውምነበር» /ዘጸ. 6፥2-3/ ተብሎ የተጻፈው ሌላው ቀርቶ « እግዚአብሔር»የሚለው ስም እንኳ ከዚያ በፊት ላሉት እንዳልታወቀያረጋግጥልናል፡፡ ስለዚህ «እግዚአብሔር»የሚለውና ሌሎች ብዙ ነገሮች ከሕገ ኦሪት በኋላእንደተገለጡ መጽሐፍ ቅዱስ ሰፊ ምስክርነትይሰጠናል፡፡ ይልቁንም ደግሞ ምሳሌያዊ/Allegorical/ በሆነ መንገድ የተገለጡትንስንመለከት እጅግ እንደነቃለን፡፡

    እግዚአብሔር ለነቢያቱም በተለያየ መንገድተገልጦላቸዋል፡፡ ለሙሴ በሐመልማል ወነበልባል/ዘጸ.3፥1/ ለኢሳይያስ በአምሳለ አረጋዊ ነዋሕ፤ /ኢሳ. 6፥1/ ለዳንኤል በአምሳለ ዕብን ቅውምከረጂም ተራራ ላይ በተፈነቀለ ትልቅ ድንጋይ / ዳን9፥ /... ለሌሎቹም በብዙ ኅብርና አምሳልተገልጦላቸዋል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ « በብዙ ዓይነትናበብዙ ጐዳና» ያለው ይህንኑ ነው፡፡ /ዕብ.1፥1/በብሉይ ኪዳን የተጻፉ መጻሕፍትን በሙሉስንመለከታቸው«እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፣እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤...» በሚል መግቢያየሚጀምሩ ናቸው፡፡ ይህም ቃልና ትምህርቱ በሙሉከእግዚአብሔርየተሰጠ እንጂ የእነርሱ ላለመሆኑበሌላ አነጋገር የመገለጥ ሃይማኖት፤ ትምህርትመሆኑን እየደጋገመ ያረጋግጥልናል፡፡ ይህም ሁሉሆኖ፤ በብሉይ ኪዳን ብዙ ነቢያት ተነሥተውቢያስተምሩም ብዙ መጻሕፍት ቢጽፉምየእግዚአብሔርአንድነትና ሦስትነት ግን እጅግምስጢራዊና ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ እንጂበግልጽ አልታወቀም ነበር፡፡ ምክንያቱም በሚገባውመንገድ ራሱን ገና አልገለጠም ነበርና፡፡

     ለአብርሃም የተገለጡት ሦስት ሰዎች፤ «ኑእንውረድ፣» የሚሉት ዓይነት ቃላትና ይህንኑከሚመስሉት ጥቅሶች በቀር በጊዜው /ብሉይዘመን/ የነበሩ ሰዎች ሁሉ ስለ እግዚአብሔርየአንድነትና የሦስት ምስጢር በበቂውአልተገለጠላቸውም፡፡ በመጽሐፈ ኢያሱየተጻፈውንና ስለ እሥራኤል የዮርዳኖስ ወንዝተሻግሮ ከምድረ ርስትን መርገጥን በተመለከተ«ሙሴም እንዳዘዛቸው የሮቤል ልጆች፣ የጋድምልጆች፣ የምናሴም ነገድ እኩሌታ ተሰልፈውበእሥራኤል ልጆች ፊት ተሻገሩ፡፡» የሚል ተጽፎአል/ኢያ.4፥17/፡፡ አንድ የጥንት የቤተ ክርስቲያን ሊቅይህን ሲተረጉመው እነዚህ ቀድመው የተሻገሩትከአሥራ ሁለቱ ነገድ ሁለቱ ነገድ በሙሉናሦስተኛው ከፊሉ መሆኑ በብሉይ ኪዳን ዘመንስለነበረው የሥላሴ ዕውቀት ምሳሌ ነው፡፡ በዚያዘመን ስለ አብና ስለወልድ በመጠኑ ስለመንፈስቅዱስ ደግሞ እጅግ በብዥታ ያውቁ ነበር፡፡ሦስተኛው ነገድ በከፊል የተሻገረው ለዚህ ነው፡፡ሦስቱ ነገድ እንኳን አለመሟላቱም በዘመኑምስጢረ ሥላሴ በከፊል በምሳሌና በጥላ ብቻይታወቅ የነበረ ስለመሆኑ አሰረጂ ነው በማለትይተረጉማል፡፡በርግጥም ቀደም ብለን እንዳየነውምየእግዚአብሔርመገለጥ እየጨመረ እየጨመረእንደመጣ መጽሐፍ ቅዱስ ምስክር ነው፡፡

    የብሉይ ኪዳን ዘመን መገለጥ እየጨመረእየጨመረ ከመጣ በኋላ ፍጹም መገለጥ ሲመጣያኛው የጥላውና የምሳሌው መገለጥይደመደማል፡፡ፍጹሙ መገለጥም የአምላክ ሰውሆኖ መገለጥ ነው፡፡ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ«መጀመሪያ ቃል ነበረ፣...» ካለ በኋላ «ለሰው ሁሉየሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣነበር፡፡ በዓለም ነበረ ዓለሙም በእርሱ ሆነ ዓለሙምአላወቀውም» ዳግመኛም ከዚያው አስከትሎ«ቃልም ሥጋ ሆነ፣ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛአደረ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብርየሆነውን ክብሩን አየን» ሲል መገለጡን አበሠረ፤ /ዮሐ 1፥1-18/፡፡ይህን መገለጥ ደግሞ እንኳንሰዎች መላእክትም ተግተው ይሹት ነበረ፡፡ ቅዱስጴጥሮስ፤ «ለእናንተ ስለሚሰጠው ጸጋ ትንቢትየተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ተግተው እየፈለጉመረመሩት፤ ለእነርሱም ከሰማይ በተላከ በመንፈስቅዱስ ወንጌልን የሰበኩላችሁ ሰዎች አሁንባወሩላችሁ ነገር እናንተን እንጂ ራሳቸውንእንዳላገለገሉተገለጠላቸው፤ ይህንም ነገርመላእክቱ ሊመለከቱ ይመኛሉ» /1ኛ ጴጥ. 1፥1-12/ ሲል እንደገለጸው፤መላእክቱ የአምላክንመገለጥ ለማየት እጅግ ጓጉተው ነበር፡፡ ምክንያቱምእነርሱም ቢሆኑ አምላክን ለማየት ዕድልየሚያገኙት ሰው ሆኖ ሲገለጥ ብቻ ነውና፡፡

    ቅዱስ ጳውሎስ፤ «እግዚአብሔርንምየመምስልምስጢር ያለጥርጥር ታላቅ ነው፡፡ በሥጋ የተገለጠ፣በመንፈስ የጸደቀ፣ ለመላእክት የታየ፣ በአሕዛብየተሰበከ፣ በዓለም የታመነ፣ በክብር ያረገ» /1ኛጢሞ.3፥16/ በማለት ለመላእክት የታየውበሥጋ በመገለጡ እንደሆነ አረጋግጦልናል፡፡እነርሱም ምስጢረ ሥጋዌን ከሰው በላይአጣጥመው ተጠቅመውበታል፡፡ በብሥራቱ ቅዱስገብርኤል ብቻ ቢሣተፍም በልደቱ ጊዜ ግን ብዙዎችመላአክት በአንድነት ለእረኞች ለማብሠርታድለዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በመዋዕለ ሥጋዌው ሁሉእየተላላኩ አምላክን ማየት ጠገቡ፡፡ ሲሰቀልናሲሞትም በአርምሞ በመደነቅ ተመለከቱ፡፡ትንሣኤውን አበሠሩ፡፡ የቀሩትም በዕርገቱ ዕለትሐዋርያትን አረጋግተው ዳግም ምጽአቱን አውጀውተሰወሩ፡፡ ዳግመኛ ሲመጣ መለከት እየነፉ ከፊትከፊት እየቀደሙ ከኋላም እየተከተሉእንደሚመጡም ተጽፎላቸዋል፡፡በዚህም ምክንያትየአምላክ መገለጥ የመላእክት ደስታ ሆነ፡፡ ስብሐትለእግዚአብሔርበሰማያት ወሰላም በምድር ስምረቱለሰብእ፤ እያሉ የዘመሩት ወድደው አይደለም፡፡ተገልጦ ባዩት ጊዜ ለመደመማቸው ወሰን ቢያጡለሰው ያለውንም ፍቅር ይገልጡት ዘንድ ቢሳናቸው፤ይህን ምስጋና እያጣጣሙ ክብርና ቅድስናቸውንለራሳቸው አስጨመሩ፡፡ ይሁን እንጂ አምላክ ሰውበመሆኑ ከረቂቃኑ መላእክት ይልቅ የበለጠየቀረቡት ሰዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ በዘመነ ብሉይእንደ ነበረው እንደ ሄኖክ፣ እንደ መልከጼዴቅ፣አብርሃም፣ ይስሐቅና ያዕቆብ፣ ዳዊትና ሰሎሞን፣ሙሴና ነቢያት ራሳቸውን የቀደሱና ያነጹ ብቻሳይሆኑ በኃጢአት የረከሱት እነ ዘኬዎስ፣ ማርያምእንተ ዕፍረት፣ መጻጉዕ፣ በዝሙት የተያዘችው ሴትናሌሎቹም ሰውነቱን ዳሰሱት፤ አብረውት በሉ ጠጡ፤. . .፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን መገለጡን በሰፊውአሰበችው፤ በተድላ በደስታ፤ በመብልና በመጠጥምጭምር የምታከብረውምለዚህ ነው፡፡ ከዚህመገለጥ በኋላ የተላኩ ሐዋርያትምየትምህርታቸውአቀራረብ ተለወጠ፡፡ እንደ ነቢያትበዚህ መንገድ አየነው፣ እንዲህ ሆኖ ተገለጠልንየሚለው ቀረና ቅዱስ ዮሐንስ እንዳለው፤ «ስለሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንናየሰማነውን በዓይኖቻችንምያየነውንየተመለከትነውንም፣ እጆቻችንም የዳሰሱትንእናወራለን፤ ሕይወትም ተገለጠ፤ አይተንማልእንመሰክርማለን፤ ከአብ ዘንድ የነበረንም ለእኛምየተገለጠውን፤የዘላለምን ሕይወትእናወራላችኋለን» /1ኛዮሐ. 1፥1-3/ እያሉለማስተማር ቻሉ፡፡

     ከዕርገቱም በኋላ ቢሆን እርሱ ከቅዱሳኑ ተሰውሮአያውቅም፡፡ ይልቁንም ከተዋሕዶ በኋላ ምንታዌየለምና /ሰው ከሆነ በኋላ መታየቱ፣ መወሰኑ፣መጨበጡ፣ መዳሰሱ አልቀረምና/ በየዘመኑይገለጣል፡፡ በየቅዱሳኑ ሕይወት እንደተጻፈው እነአባ ብሾ/ሶ/ይ እግሩን አጠቡት፣ አዘሉት፡፡ በየዕለቱለሰማዕታቱ እየተገለጠ አጸናቸው፤ ጻድቃኑንምምስጢሩን አብዝቶ ገለጠላቸው፡፡በየገድላቱም ላይቅዱሳኑ ሲያርፉ «ይህን ያህል ቅዱሳኑን አስከትሎመጣ፤ ነፍሱንም ተቀበለ፣. . .» የመሳሰሉትአገላለጾች ምንኛ ግሩም ናቸው፡፡አንድጊዜ ሰውሆኖአልና እንደቀድሞው ለነቢያቱ እንዳደረገውሳይሆን አሁን በሥጋ ተገልጦአልና በየጊዜውይመጣል፣ ይታያል፣ ይጨበጣል፤ይዳስሳቸዋል፤ይስማቸዋል፤ ያወጋቸዋል፡፡ ቅዱስጴጥሮስን በሮማ አደባባይ «ወዴት ትሔዳለህ?»ብሎ እንደመለሰው፤በየዘመኑ እየተገለጸይመራቸዋል፤ ያነጋግራቸዋልም፡፡ መገለጥ፤ግሩምና ድንቅ መገለጥ፤ ሃይማኖቱም የመገለጥ፡፡እርሱ ራሱ «ይህ ዛሬ እናንተ የምታዩትን ብዙ ነቢያትሊያዩ ወደው አላዩም፤ እናንተ የምትሰሙትን ሊሰሙወድደው አልሰሙም፤ የእናንተ ግን ያዩ ዓይኖቻችሁ፤የሰሙ ጆሮቻችሁ የተመሰገኑ ናቸው» እንዳለ ፤የሐዲስ ኪዳን፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታት፣ ባሕታውያንስውራን ሁሉ ምን ያህል የተመሰገኑ ናቸው፡፡በየዕለቱ ጌታቸውን ያዩታልና፤ ለዚህምተጠርተዋልና፡፡

    ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ልዩየሚያደርጋት ብቻ ሳይሆንከትክክለኛነቷማረጋገጫዎች አሁንም ዋነኛዋመገለጡ ነው፡፡ የሌሎቹ በተለይምከኢንዱስትሪውአብዮት በኋላ የተነሡ የክርስትናክፍልፋዮች/Denominations/ ሁሉ መሠረተእምነታቸው የሚዋቀረው በዩኒቨርስቲዎችናበየተቋማቱ ባሉ ምሁራኖቻቸው አስተምህሮበጠረጴዛ ዙሪያ ነው፡፡ የኦርቶዶክሳዊትተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ የሚመሠረተው ግንበገዳማውያን ቅዱሳን መገለጥ ላይ ነው፡፡ ከጥንትጀምሮ እስካሁን ሊቃውንቱ ሁሉ በመማር ብቻሳይሆን በገዳም ተወስነው፣ ሱባኤ ገብተው፣በእርሱ መገለጥ የተሰወረ ምስጢርይገለጥላቸዋል፤የረቀቀው ይጎላላቸዋል፡፡ ያንን ብቻያስተምራሉ፤ እርሱንም ብቻ ይዘንእናስተምራለን፤በተገለጠውም መሠረት እንኖራለን፡፡በእኛ ሀገር እንኳን እነ ቅዱስ ያሬድ፤ አባ ጊዮርጊስ፣አባ ዜና ማርቆስ፤ አባ ተክለሃይማኖት፣. . . ሁሉምበሱባኤ፣ በገዳም፣ በምናኔ፣ በተጋድሎ ተወስነው፤በተገለጠውና በሚገልጥላቸውመንገድ ብቻ ተጓዙ፡፡ቅዱሳት መጻሕፍትም የሚያረጋግጡልንይህንኑ ብቻነው፡፡

    ሃይማኖትን እንቀበለዋለንከዚያም እንጠብቀዋለንእንጂ ልንሠራው አንችልም፡፡ የያዕቆብ ወንድምቅዱስ ይሁዳ «ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉእየመከርኋችሁእጽፍላችኋለሁ» /ይሁ.1፥3/ ሲልእንደገለጸልን፤ሃይማኖት ለቅዱሳን በመገለጥየተሰጠች እንጂ የተሠራች አይደለችም፡፡ጌታችንምበወንጌል «ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህንገለጥሁላቸው፡፡የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤ቃልህንም ጠብቀዋል፡፡ የሰጠኸኝን ሁሉ ከአንተእንደሆነ ያውቃሉ፤ የሰጠኸኝ ቃልሰጥቻቸዋለሁና፤እነርሱም ተቀበሉት. . .» /ዮሐ.17፥22/ ሲል እንዳስተማረው፤ክርስትናየተቀበልነውና የምንጠብቀው እንጂ የሠራነውናየምናሻሽለው አይደለም፡፡ በዚያ ጊዜያልገለጸልንንም«የምነግራችሁ ብዙ ነገር አለ፤ አሁንግን ልትሸከሙት አትችሉም፤ መንፈስ ቅዱስ በመጣጊዜ ግን እርሱ ሁሉንም ያሳውቃችኋል» የሚልተስፋን ሰጠን፡፡ መንፈስ ቅዱስም ከእኛ ጋርየሚኖረውም እስከ ዕለተ ምጽአት መሆኑንአረጋገጠልን፡፡ስለዚህም እስከ ዛሬ ድረስመንፈሳቸውን ላላረከሱት በየጊዜው ይገለጣል፡፡ለሐዋርያት ገለጠላቸው፤ ለሊቃውንት ገለጠላቸው፤ለጻድቃን በየገዳሙ ገለጠላቸው፤ለየመምህራኑምበየሱባኤያቸው በተቀደሱጉባኤዎቻቸው ገለጠላቸው፤ እኛም የተገለጠውንይዘን እርሱንም እየጠበቅን እንጓዛለን፡፡ከተገለጠውውጭ መጓዝም የተወገዘ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ፤«ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክከሰበክንላችሁወንጌል የሚለይ ወንጌልንቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን» /ገላ.1፥8/ በማለትአረጋገጡልን፡፡

    ስለዚህም በዘመነ አስተርእዮ ይህን የአምላክንመገለጥ እና የመገለጥን ሃይማኖትየምንዘክርበትምክንያት፤ ሃይማኖት ሰዎችያልፈጠሩት ነገር ግን በአምላክ መገለጥና እርሱበገለጠው ሃይማኖታዊ ዕውቀት ብቻ መጓዝንማዘከር መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡

    በተገለጠልን ጸንተን ለቅዱሳን የተሰጠችውንሃይማኖት ተጉዘንባት ለልጆቻችንም አውርሰናትናጠብቀናት እንድናልፍ የእግዚአብሔርቸርነትየድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን፤

    በዓሉን በዓለ ሰላም ፤ በዓለ ክብር ፤ በዓለ ፍስሐ ያድርግልን - አሜን፡፡

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: የመገለጥ ሃይማኖት በአስተርእዮ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top