• በቅርብ የተጻፉ

    Wednesday 11 November 2015

    ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን


    ሙሴአሮንንና ሖርምን ከተማዋን እንዲጠብቁአድርጎ ኢያሱን አስከትሎ ወደ ደብረ ሲናሔደ። ኢያሱን ከተራራው ግርጌ ትቶ ሙሴብቻውን ወደ ሲና ወጣ። በሲና ተራራም 40ቀንና ለሊት ቆየ።

    በዚህን ጊዜ እስራኤላዊያን ተስፋ ቆረጡናማጉረምረም ዠመሩ። “ፀሐይ ወጣች ገባችሙሴ ግን ቀለጠ” አሉ። አመሌ አመሌ ሲልበደብረ ሲና ያያት እሳት አቃጠለችው እንዴ?ሐመልማሉንስ አላቃጠለች ሙሴን ፈጀችውእንዴ? ይህ ባይሆንም ወደኛ ሲመጣ ባሕረኤርትራን ሲሻገር ሰጠመ እንዴ? ብለውአጉረመረሙ

    አንገተ ደንዳና የተባሉት እስራኤላዊያን በሬአላርስ ሲል አንገቱን እንደሚያደነድንአንገታቸውን አደንድነው ካህኑ አሮንን ሙሴስለቀረ አምላክም ስለሌለ ጣኦት ስራልንብለው ጮኹ። አሮን አሮን ግበር ለነአማልክተ ዘይሐውሩ ቅድሜነ እያሉ ጣኦቱይሰራላቸው ዘንድ ካህኑ አሮንን አቻኮሉትአጣደፉትም። ይገርማል! እኛም አንዳንዴካህናቱን የማይገባ ሥራ ስሩ እንደምንላቸውማለት ነው። ካህናቱን ፣ መነኮሳትን ፣ ጳጳሳትን፤ ባሕታዊያንን ዓለማዊ ስራ ስሩእንደምንላቸው እስራኤላዊያንም ካህኑንጣዖት ስራ አሉት።

    አሮንልቡ ተከፈለ። ጣኦቱን ቢሰራ ከፈጣሪ ሊጣላባይሰራ እስራኤላዊያን በድንጋይ ሊወግሩትመኾኑን እያሰበ ልቡ ተከፈለ። በመጨረሻምዘዴ መጣለት። አፍቃሬ ንዋይ ናቸውናወርቃችሁን አምጡ ብላቸው ይሰስታሉ ብሎአሰበ። ይኹን እንጂ በልባቸው ያደረውሰይጣን እጃቸውን ፈቶ ወርቁን በአሮን እግርአስቀመጡ። ካህኑም መሬት ተቆፍሮ ቢቀበርጣኦት ይኾናል አላቸው በዚያው ጠፍቶየሚቀር መስሎት። ግና የተቀበረው ወርቅበግብረ ሰይጣን አንገቱ ወርቅ ደረቱ ብርእግሩ ብረት የኾነ ጥጃ ኾኖ ወጣ።

    እስራኤላዊያንም አምላካችን እያሉ መጮኽዠመሩ። ቀን ሲደርስ አንባ ይፈርስ እንዲሉሙሴ ከሲና ተራራ የሚወርድበት ቀን ደረሰ።ጽላቱን ከእግዚአብሔር ተቀብሎ 40 ቀንሙሉ ከሲና ተራራ ግርጌ የነበረውንትዕግስተኛ ኢያሱን አስከትሎ ወደ ሕዝበእስራኤል መጣ። ነቢዩ ሙሴ ከሲና ተራራላይ የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዞ ሲወርድእስራኤላዊያን ጣኦትን ያመልኩ ነበር፤

    ሙሴ ከሲና ተራራ መውረዱ .... ጌታችንከሰማየ ሰማያት የመውረዱ ምሳሌ ነው።    

    ታቦቱ ከሙሴ እጅ ወድቆ ጣዖታቱን ሰባበረ...... ይህም ጌታችን የዲያቢሎስን እራስእራሱን የመቀጥቀጡ ምሳሌ ነው።

    ጌታ ስለ ኃጢአታችን በፈቃዱ ሞቶ ሞትንድል አድርጎ ተነሣ “በክብርም ዐረገ” ይህምታቦቱ ከእንደገና በእግዚአብሔር ጣት ተጽፎለሙሴ የመሰጠቱ ምሳሌ ነው!!!  ዘፀአትምዕ. 31-34

    ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶበተነሣ በአርባኛው ቀን ጌታችን የዐረገው ማታ ማታ እየወጣ የሚያድርባት፣ ሐሙስሌሊት በይሁዳ በኩል ለአይሁድ ተላልፎየተሰጠባት፣ ሐዋርያት ስለ ነገረ ምጽአትጠይቀው በተረዱባት ተራራ ደብረ ዘይትነው። በዚህች ተራራ ላይ ብዙ የወይራ ተክል ስለሚገኝ ተራራው ደብረዘይት ተብሏል።

    ጌታችን ከትንሳኤ “እስከ ዕርገቱ ለ40 ቀናት”ለሐዋርያቱ እየተገለጸ ያስተምራቸው ነበር።[ሐዋ. 1:3] ነገር ግን ምን እንዳስተማራቸውአልተጻፈም; በመፅሐፈ ኪዳን ላይ ግንተፅፏል። ቤተክርስቲያናችን አዋልድመጽሐፍትን የምትጠቀመው በእንዲህ ሁኔታነው ማለት ነው።

    ዐርገ የሚለው የግዕዝ ግስ ዐረገ፣ ወጣበሚሉት የአማርኛ ቃላት የሚፈታ ሲሆንዕርገት የሚለው ስምም ማረግን፣መውጣትን፣ አወጣጥን ያመለክታል።/አ.ኪ.ክ መ.ቃ/ አስቀድሞ ክቡር ዳዊትእንደተናገረው መድኃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ ደቀመዛሙርቱ እያዩት ወደ ሰማይዐርጓል። "ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ፤ወእግዚእነ በቃለ ቀርን" እንዲል መዝ. 46፥5ጌታችን በእውነት እንዳረገ ይኽም ሊታመንየማይችል እንዳልሆነ የቤተ ክርስቲያን ሊቅቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ያስረዳል። ሕማምየሚስማማው ግዙፍ ሥጋን ተዋሕዶ ሳለከስቅለቱ አስቀድሞ በባሕር ላይ ከሄደ፡ ዛሬነፋስን ከፍሎ ሲያርግ ቢታይ ማንም ማንአይጠራጠር፤ሥጋው አልተለወጠምና። /ሃይማኖተ አበው ዘዮሐ.አፈ.ክፍል 13 ቁጥር15/

    አንቃዕድዎተ ዐይን

    ወዘንተ እንዘ ይብሎሙ ተለዐለ ወነሥአቶደመና ወዐርገ ሰማየ እንዘ እሙንቱ ይኔጽሩኀቤሁ ወተሠወረ እምአዕይንቲሆሙ። የሐዋ. 1፥9 አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ ወደ ሰማይ የወጣውበርህቀት(በመራቅ) እንጂ በርቀት (ቀ-ጠብቆይነበብ፤ ረቂቅ በመሆን) አይደለም።ይኽምማለት አስቀድሞ የተዋሐደውን ሥጋ አርቅቆ፣ግዙፍነቱን አጥፍቶ ሳይሆን ከመለኮቱ ጋርበተዋሕዶ አንድ የሆነው ግዙፍ ሥጋግዝፈቱን ሳይለቅ ከዐይን በመራቅ፣ ከፍ ከፍበማለት፣ ወደ ሰማይ በመውጣት ነው።

    በትምህርቱ የተጽናኑ፣ በተአምራቱ የተማረኩ፣ትዳራቸውን፣ ወላጆቻቸውን፣ ሃብታቸውን፣ ሥልጣናቸውን፣… የተዉለት ሐዋርያትለሦስት ዓመት ከሦስት ወር አብሮአቸው የቆየኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ሲለያቸው በናፍቆትተይዘው ወደ ሰማይ ሲወጣ ትኩር ብለውተመለከቱት። ያሳያቸውን ፍቅር፣ ሑሩወመሃሩ በማለት ያዘዛቸውን አገልግሎትእንዴት እንደሚወጡት እያሰቡ ትኩር ብለውተመለከቱት።

    ነቢር በየማነ አብ

    ነቢር በየማን (በቀኝ መቀመጥ) በመጽሐፍቅዱስ አገባብ መሠረት ዕሪናን (በሥልጣንአንድ መሆንን) ያመለክታል። በመለኮቱየእግዚአብሔር አብ ልጅ፣ በትስብእቱ (ሥጋንበመዋሐዱ) የማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስካረገ በኋላ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።ማር.16፥19

    ይኽ ስለ መለኮት የተነገረ አይደለም፤በመለኮቱስ ከአብ ሥልጣን ዝቅ ያለበትየዐይን ጥቅሻ ያህል ጊዜ የለምና። ነገር ግንከተዋሕዶ በፊት ደካማ፣ በደለኛ እና ውርደትይስማማው የነበረው የእኛ ሥጋ ከተዋሕዶበኋላ ጸጋን የሚያድል፣ እውነተኛ ፍርድንየሚያደርግ፣ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርእኩል ሥልጣን ያለው እውነተኛ አምላክእንደሆነ ለመግለጽ ነው።

    ዕርገተ ልቡና

    ሲጸልዩም ሆነ ሲናገሩ፣ ሲጾሙም ሆነሲመገቡ፣ ሲሠሩም ሆነ ሲያርፉየአምላክዎን ውለታ በማሰብ በሃያ አራትሰዓት ውስጥ ለምን ያህል ደቂቃዎችያርጋሉ(ይመሰጣሉ)? ሐዋርያት ጌታችንበአካለ ሥጋ አብሮአቸው እያለ ያዘዛቸውንትዕዛዝ ለመፈጸም እስከ ሕይወት ፍጻሜድረስ በመታመን አደራቸውን እንደተገበሩሁሉ በሐዲስ ኪዳን ያለን ምዕመናንምጌታችን በበረት በመወለድ፣የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠብ የሰጠንንየትሕትናን አደራ፤ወደ ግብፅ በመሰደድ፣በመስቀል በመቸንከር ያሳየንን መከራንየመቀበል አደራ፤ አልአዛርን ከሙታንበማንሣት፣ ራሱም በገዛ ሥልጣኑ ከሙታንበመነሣት የነገረንን ትንሣኤ ዘጉባኤን ተስፋየማድረግ አደራ በሐሳባችን እያረግን ፣ልባችንን ከፍ ከፍ እያደረግን ክርስቲያናዊምግባራትን ከሃይማኖት ጋር አስተባብረንበመያዝ ልንጠብቀው ይገባል።

    በዕርገቱ ዕርገተ ልቡናን ያድለን።

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top