• በቅርብ የተጻፉ

    Monday 9 November 2015

    ቤተክርስቲያን እንዴት ተመሠረተች ? ክፍል ፩

    ስለ ክርስትና ሃይማኖት ስለ ቤተክርስቲያንበምንናገርበት ጊዜ ሁሉ ትዝ የሚለንናየምናስተውለው የመጀመሪያው ሰው የአዳም ሁኔታነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን እግዚአብሔርየሁላችንን አባት አዳምን በአርአያውና በመልኩከፈጠረው በኋላ ባረከው፡፡ ኹሉንም እንዲገዛሥልጣን ሰጠው፡፡ በረከቱን ሥልጣኑንና ሲሳዩንከሰጠው በኋላ ፈጣሪውን የሚያስታውስበት ትእዛዝአዘዘው፡፡ እሱ ግን በተሳሳተ ምክር ተመርቶከፈጣሪው ትእዛዝ ወጣ፡፡ በዚህ ጊዜ የሞት ፍርድተፈረደበት፡፡ ይህም የሞት ቅጣት ለርሱ ዐቅምቀላል አልነበረም፡፡ በሱም ብቻ አልቀረም የልጅልጆቹ ይህን የሞት ቅጣት በውርስ ተካፈሉት፡፡ የዚህየሞት ጽዋ ተካፋዮች ሆኑ፡፡ የአዳም ሕግንመተላለፍ የልጆቹም ተባባሪነት በእግዚአብሔርናበነሱ መካከል ያለውን ልዩነት እያሰፋው ሔደ፡፡የፈጠራቸው እግዚአብሔርን ዘንግተው የሰማይናየምድርን ሠራዊት ማምለክ ጀመሩ፡፡ በጨረቃ፣በፀሐይና በከዋክብት፣ በእሳት፣ በውኃ፣ በእንስሳትናበአራዊት፣ በዛፍና በተራራ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔርየሰውን ዘር ጨርሶ ለመደምሰስ ስላልፈለገ ይህንየሰው ልጅ መራራና አሰቃቂ ታሪክ ከመጀመሪያውጀምረው ሲከታተሉ የነበሩ በአንድ አምላክ በማመንየታወቁ ጥቂት ሰዎችን አተረፈ፡፡ እነሱም ከአበውሄኖክን፣ ኖህን፣ አብርሃምንና ሎጥን ሌሎችንምየመሳሰሉትን ነው፡፡ 

    ከአብርሃም ይስሐቅ፣ ከይስሐቅ ያዕቆብ ተወለደ፡፡ከያዕቆብም አሥራ ሁለት ልጆች ተወለዱ፡፡ አሥራኹለቱን የእሥራኤል ነገድ መሠረቱ፡፡ ለነሱምአንዳንድ ጊዜ ራሱ እግዚአብሔር እየተገለጠአንዳንድ ጊዜም በነቢያትና በካህናት አማካይነትሕጉንና ትእዛዙን ይሰጣቸው ነበር፡፡ መላልሶተአምራት ያደርግላቸው ነበር፡፡ ነገር ግንበአካባቢያቸው በነበረው የአረማውያን ተጽዕኖምክንያት እነዚህ ሰዎች አልፎ አልፎ በየጊዜው ወደአምልኮ ባዕድ ይወድቁ ነበር፡፡ በአንድ ወገን ይህሲሆን በሌላው ወገን ሲታይ ደግሞ ከእውነተኛውየአንድ አምላክ እምነት ያላፈነገጡ፤ በአምልኮባዕድ ያልተለወጡ ብዙ እሥራኤላውያን ነበሩ፡፡እነዚህ አምልኮታቸው የጸና ነበር የሚባሉትእሥራኤላውያን ከኃጢአት ለመንጻትናየእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ ለመጠየቅ ብዙወይፈኖችንና ጊደሮችን ይሠዉ ነበር፡፡ እግዚብሔርንደስ ቢለው በማለት በወርቅ የተለበጠ በሐርየተጨመጨመ ቤተ መቅደስ በሰሎሞን ተሠርቶነበር፡፡እግዚአብሔር በነቢያት እያደረ የሚመልሰውመልስ ይህን ሁሉ ደስ ብሎት የተቀበለውአለመሆኑን የሚገልጽ ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ የሰው ልጅየታሪክ ጉዞ በኋላ እግዚአብሔር በራሱ ፈቃድየሰውን ልጅ ለማዳን የቀጠረው ቀን ሲደርስ ልጁንሰው ይሆን ዘንድ ላከው፡፡ በልጁ በክርስቶስ ሞትቤተክርስቲያን ተመሠረተች፡፡ 

    ቤተክርስቲያን የተወለደችው ወይምየተመሠረተችው በፍልስጥዔም ምድር ነው፡፡ይህም የሆነበት ምክንያት ከላይ እንደተገለጠውየሰውን ልጅ ትክክለኛ ታሪክና ሃይማኖት የያዙየእግዚአብሔርንም የምሕረት ቀን በተስፋሲጠባበቁ የነበሩ በትዕግሥታቸው የተመሰገኑ ብዙደጋግና ቅዱሳን ሰዎች ስለነበሩባት ነው፡፡የእግዚአብሔርንም የማዳን ሥራው ድንገተኛሳይሆን ለብዙ ዘመናት በተስፋ ሲጠበቅ የቆየመሆኑን ለመግለጥ ነው፡፡ የክርስትና ሃይማኖትየታሪክ ሃይማኖት ነው መባሉም በዚህነው፡፡ ክርስትና በተወለደበት ጊዜ የነበረውንየፍልስጥኤም ሁኔታ ለማጤን የሚቻለው ቀደምካለው ሁኔታ የጀመርን እንደሆነ ነው፡፡ ፍልስጥዔምየአብርሃም የቃልኪዳን አገር ከነዐን ናት፡፡ በሌላምአነጋገር ምድረ ርስት ትባላለች፡፡ መጽሐፍ ቅዱስእንደሚነግረን የያዕቆብ ልጆች በሙሉ ከዚች አገርተሰደው በግብጽ በባርነት ይኖሩ ነበር፡፡ ዘመኑም17ዐዐ-13ዐዐ ከጌታ ልደት በፊት መሆኑ ነው፡፡ከጌታ ልደት በፊት 13ዐዐ ዓመት ገደማ በሙሴመሪነት ወደዚች አገር ተመልሰዋል፡፡ በ1922 ዓመትከጌታ ልደት በፊት አሥራ ኹለቱ ነገድ ባገዛዝተጣልተው ለሁለት ተከፈሉ፡፡ አሥሩ ነገድ በሰሜንፍልስጥኤም በሰማርያ ተቀመጡ፡፡ 

    ከተማቸው ሴኬም ነበረች፡፡ ኹለቱ ነገድ ደግሞበደቡብ ፍልስጥኤም ሰፈሩ፡፡ ከተማቸውምኢየሩሳሌም ነበረች፡፡ በ792 ዓመት ከጌታ ልደትበፊት ሰሜኑን ክፍል እስራኤላውያን በስልምናሶርመሪነት መጥተው አጠፏት፡፡ ሕዝቡም ተማረኩ፡፡ይህ ሲሆን በደቡብ ክፍል የነበሩት የተማረኩትንአሥሩን ነገድ እንደ ጠላት ይቆጥሯቸው ስለነበርሳይደሰቱ አልቀሩም፡፡ ነገር ግን በ586 ከጌታ ልደትበፊት የሴኬም ፅዋ በኢየሩሳሌምም ደረሰ፡፡በናቡከደነፆር መሪነት ባቢሎናውያን መጥተውኢየሩሳሌምን አጠፉ ሕዝቡንም ማርከው ወሰዱ፡፡ሰባ ዓመት በምርኮ ቆይተው ከተመለሱ በኋላጥቂት እንደቆዩ በፋርስ ተወረሩ፡፡ 
    አሁንም እንደገና በ33ዐ ከጌታ ልደት በፊት ግሪኮችበዚች ምድር ላይ ቅኝ ገዢዎች ሆኑ፡፡ በመጨረሻም63 ዓመት ከጌታ ልደት በፊት ሮማውያን ተረከቧት፡፡እንግዲህ በዚህ ረጅም የተፋልሶ ጊዜ ሕዝቡ ብዙየባህልና የሃይማኖት ቀውስ ደርሶበታል፤እስራኤላዊ ያልሆኑ ጠባዮችንም ሳያውቀውሸምቷል፡፡ ክርስትና በፍልስጥኤም ሲመሠረትየነበረውን ሁኔታ ለማወቅ የሚቻለው ይህ ሲታይነው፡፡ ክርስትና ሲወለድ ምድረ ፍልስጥኤም እንደሌሎቹ የመካከለኛው ምሥራቅ የሰሜን አፍሪካናየታናሽ እሲያ አገሮች በሮም ቅኝ ግዛት ሥር ነበረች፡፡በውስጥም የነበሩ ሕዝቦችም የተከፋፈለየሃይማኖትና የፖለቲካ ቡድን ነበራቸው፡፡ ከነዚህምዋናዎቹ የፈሪሳውያንና የሰዱቃውያን ቡድኑችነበሩ፡፡ የሰዱቃውያን ቡድን የሀብታሞችና የካህናትቡድን ነው፡፡ ይህ ቡድን ለባሕል፣ ለሥነ ሥርዓትናለሃይማኖት ግድ የሌለው ከቅኝ ገዢዎች ጋርተስማምቶ በነሱ ሥልጣኔ መጠቀምን ብቻ እንጂየነቢያትን ትንቢትና ሌሎችንም የብሉይ ኪዳንመጻሕፍት አይቀበሉም ነበር፡፡ የሙታንን ትንሣኤናየመሲሕንም መምጣት አያምኑም ነበር፡፡ ሌላውቡድን የፈሪሳውያን ቡድን ነው፡፡ 

    ፈሪሳዊ “ፖርሽ” ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የወጣነው፤ ትርጉሙም “የተለየ” ማለት ነው፡፡ እነዚህፈሪሳውያን ምንም የቅኝ አገዛዝ ቀንበር መላልሶቢያደቃቸውም ባህልና ልምዳችን አይነካበሃይማኖትም የሙሴን ሕግና የነቢያትን መጻሕፍትየምንጠብቅ እኛ ብቻ ነን ባዮች ነበሩ፡፡ ስለዚህከአይሁድ ዘር ውጭ ከሆነ ከማንኛውም ጎሳና ዘርጋር በባህልና በሥልጣኔ መቀራረቡን እንደመርከስና ሕግን እንደመተላለፍ ይቆጥሩ ነበር፡፡የመሲሕንም መምጣት ነቅተውና ተግተውይጠባበቁ ነበር፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያታቸውሀገራቸው ፍልስጥኤምን ከሮም ግዛት ነጻለማውጣት የቆየ ጉጉት ስላላቸው ነው፡፡ እንደነሱአስተሳሰብ መሲሕ ሲመጣ የጦር ኃይል አቋቁሞራሱ የጦር መሪ በመሆን የሮማን የቅኝ ግዛት ቀንበርአውልቆ ጥሎ የዳዊትን ቤተ መንግሥት የሚያድስመሲሕ ይጠባበቁ ነበር ማለት ነው፡፡ ምንም እንኳከትንሣኤ በኋላ ሥጋዊ ኑሮ አለ ብለው ቢያምኑምትንሣኤ ሙታን መኖሩን ያውቁ ነበር፡፡ ፈሪሳውያንበዕለታዊ ኑሮአቸው ብዙ ሀብት ፍልስጥኤምን ነጻያወጣል የሚለውን የፈሪሳውያን እምነትና ተስፋበመቃወም ሌላ ንኡስ ቡድን ከፈሪሳውያንተከፍለው በሙት ባሕር አካባቢ ገዳም መሥርተውይኖሩ ነበር፡፡ የእነሱም ዓላማቸው እንደ ፈሪሳውያንመሲሕን መጠባበቅ ነው፡፡ ኤሤይ በመባልየታወቁት እነዚሁ ክፍሎች ከፈሪሳውያን የሚለዩትፈሪሳውያን በጦር ኃይል ነጻ እንወጣለን ሲሉ ኤሤይየሚባሉት ደግሞ በተአምራት በእግዚአብሔር ኃይልፍልስጥዔም ነፃ ትወጣለች ብለው ያምኑ ነበር፡፡በቤተልሔም በስተደቡብ ልዩ ስሙ ኩምራንበሚባል ቦታ የሚኖሩ እነዚህ ሰዎች መጻሕፍትንበመጻፍ ጸሎትን በማድረስ ብዙ ጊዜ ቆይተዋል፡፡ኤሤዎችና ፈሪሳውያን ባንድ አንድ አስተሳሰብቢለያዩም መሲሕ መምጣቱንና የተወሰኑ ምርጥጎሳዎችን ነጻ እንደሚያወጣ ዓለም አቀፋዊመሲሐዊ መንግሥት እንደሚያቋቁምና እነሱምየመንግሥት ባለሟሎች እንደሚሆኑ ሁለቱምቡድኖች ያምኑ ነበር፡፡ በእስራኤል የሃይማኖትናየነገድ ቤተሰብ ውስጥ ይህ ልዩነት ተፈጥሮመከራቸውን ሲያዩ በፍልስጥኤምና ከፍልስጥኤምውጭ የነበረው የሮማ መንግሥት ፖለቲካ ደግሞከቅኝ ግዛቱ የተነሣ ያነገንግ ነበር፤ የነጻ አውጭግንባሮች በየጊዜው የሕዝብ ቆጠራ እንዲደረግ ታዞነበር፡፡
    Source: http://www.melakuezezew.info/ 

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: ቤተክርስቲያን እንዴት ተመሠረተች ? ክፍል ፩ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top