• በቅርብ የተጻፉ

    Thursday 12 November 2015

    ዳክርስ


           ፀሐይ ብርሃኗ ነጥፎ የበርባኖስ ክንብንብ ስታጠልቅ

          ጨረቃ በሀዘን ተዉጣ በደም አበላ ስትጠመቅ

         ተፈጥሮ ስርዓቷ ተዛብቶ ቀኑ በጽልመት ሲቀየር

          አለታት በፍርሀት ተንጠዉ በድን አካላቸዉን ሲንሞሱ

          ወዳጅህ ልቡ ተነክቶ አንተን  ለድህነት ሲጠራህ

          ህይወት በቀኝህ ተሰቅሎ የቀለጠ ፍቅሩን ስታይ

          በመጨረሻዋ ደቂቃ ህይወትን መዋጀት ሲገባህ

          ታአምሩን በአይኖችህ እያየህ ቃሉን በጀሮህ እየሰማህ

           ምን የሚሉት ፈሊጥ ነዉ ይኼ በበደል ላይ በደል ማከል

           ልብን ተራራ አሳክሎ አንደበትን ለስድብ ማሾል

          ልብህ ባለማመን እረግረግ በክህደት አረንቋ ተጣለ

          ዋ! ምነዋ! ዳክርስ የእምነት ቋጥህ ሟጠጠ

                                  

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: ዳክርስ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top