• በቅርብ የተጻፉ

    Sunday 25 October 2015

    ግዑዙ ከበሮ

    ሁለት ወራት ሙሉ እጥፍ ቅልጥፍ ብሎ                

    በጾምና ጸሎት ከስራው ተገሎ               

     በሐዘን በድማሜ ዘወትር አዘንብሎ                

    የቆየው ከበሮ ዛሬ ዜና ሰማ               

     የራቀው ቅላጼው በእርጋታ ተሰማ               

     ከሩቅ አስተጋባ በሚነሽጥ ዜማ                

    ድምፁ ከአጽናፍ ዓለም ፈሰሰ በግርማ               

     በአምሳለ ኢየሩሳሌም በቅድስቲቷ ከተማ                

    ግዑዙ ከበሮ እንዲህ ከመጠቀ                

    በሁዳዴ ተኝቶ ትንሣኤን ካወቀ               

     የሰው ልጅ ምን ነካው እንቅልፉ ጨመረ                

    በትንሣኤው ማግስት እንደተኛ ቀረ።

     

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: ግዑዙ ከበሮ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top