• በቅርብ የተጻፉ

    Monday 9 November 2015

    “ቃልም ሥጋ ሆነ” [ ዮሐ 1-1 ]

    እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን!

    የጌታችንን ልደት ከብሥራት አንሥቶ በሰፊው የተረከልን ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስነው፡- “በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች”በማለት የልደቱን ዘገባ ይጀምራል፡፡ በወቅቱ ዓለምን ሁሉ የምትገዛው ሮም ነበረች፡፡ንጉሠ ነገሥቱም ቄሣር በሚል መዐርግ ይጠራ ነበር፡፡ መንበሩም ያለው በሮምሲሆን ዓለሙንም የሚያስተዳድረው በአጥቢያ ነገሥታት በኩል ነው፡፡ ንጉሠ ነገሥቱዓለሙን የሚገዛው ከመንበሩ ሳይንቀሳቀስ ነው፡፡ በመልእክተኞቹ አማካይነትዓለሙን ይገዛል፡፡ ጌታችን የተወለደው ከዘመን መርጦ በሮም አገዛዝ ዘመን ነው፡፡የሮም አገዛዝ ለእግዚአብሔር መንግሥት ገላጭነት አለው፡፡ ይኸውም፡-እግዚአብሔር አብ ከሥፍራው ሳይናወጥ ይኖራል፤ ቃሉን ወይም ልጁን እንዲሁምመንፈስ ቅዱስን እየላከ ዓለምን ይገዛል፡፡ ወደዚህ ዓለም በሥጋ የመጣውእግዚአብሔር ወልድ ነው፡፡ እርሱ ካረገ በኋላም መንፈስ ቅዱስ መጥቷል። ክርስቶስበትምህርቱ፣ በቤዛነቱ ዓለሙን ገዛ፡፡ መንፈስ ቅዱስም በጸጋው በተአምራቱእንዲሁም በክርስቶስ ቃሎች ዓለምን ይገዛል፡፡ እንዲህ ሲሆን ግን የሥላሴመንግሥት አንዲትና እኩል ናት፡፡ 

    ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤልትለዋለች [ኢሳ. 7.04]

    በጥሊሞስ ፈላደልፈስ &2ሊቃውንትን በአሌክሳንድርያ አካባቢ በምትገኘውበፋሮስ ደሴት ላይ በ72 ቀናት ውስጥ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ከዕብራዊያን ወደጽርእ /ግሪክ/ እንዲተረጎሙ አደረገ። ከ&2ቱ ሊቃውን ሁለቱ መንገድ ላይ ሲሞቱሌሎቹ ሊቃውንት ብሉይ ኪዳንን ለመተርጉም እየገሰገሱ ንጉሥ  በጥሊሞስጋርደረሱ!

    ከደረሱት  & ሊቃውንት አንዱ አረጋዊ ስምኦን ነው። እነሆ ሰባው ሊቃውንት በሙሉየየራሳቸውን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በእጆቻቸው ይዘዋል፤ አሁን ሊተረጉሙብዕራቸውን ሁሉም ያዙ! 

    ለአረጋዊ ስምኦን የደረሰው የብሉይ ኪዳን ወንጌል እየተባለ የሚታወቀው “ትንቢተኢሳይያስ” ነበር። ሊቁ አረጋዊ ስምኦንም እነሆ ትንቢተ ኢሳያስን ሊተረጉም ፩ዱብሎ ጀመረ። እስከ ፯ኛው ምዕራፍ በደህና ደረሰ፤ ምዕራፍ ፯ ላይ ሲደርስ ግን ሊቁግራ ተጋባ! እንዴት ሊሆን ይችላል እያለ ተገረመ! ምን ይሆን ያነበበው? 

    “ ናሁድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወይሰመይ ስሙ አማኑኤል” ይህችን ቃልአነበበና አሁንም ሊቁ ተደመመ!!! እንዲህ ማለት ነበርና፦

    ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤልትለዋለች [ኢሳ. 7.04]

    ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች! ከዚህ በፊት ሆኖ አያውቅም፤ በግዜውምአልተደረገም ወደፊትም አይደገምም አለና ሊቁ አሁንም ተደመመ! አሁን ድንግልበድንግልና ትፀንሳለች ብዬ ብተረጉመው አይደለም በጥሊሞስ የአሕዛብ ንጉሥቀርቶ የእስራኤል ንጉሥ ቢሆንስ ያምነኛልን? ብሎ ሊቁ አሰበ። እናም ድንግልትፀንሳለች የሚለውን ሰርዞ ሴት ልጅ ትፀንሳለች ብሎ ፃፈው። ሊቁ ስምኦን እስከ፯ኛው ምዕራፍ ስለፃፈ ደከመው መሰል ሸለብ አደረገው። 

    ትንሽ እንዳረፈም ነቃ፤ ካቆመበት ሊቀጥል ቢል እነሆ የሰረዘው ተመልሶ “ድንግልበድንግልና ትፀንሳለች” የሚለውን አነበበ። በጣም ደክሞኛል ማለት ነው?የሰረዝኩት መስሎኝ ነበር አለና አሁንም ደግሞ ሰረዘውና አሸለበ። እንዲህ እያለ“ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች” የሚለውን  ፫ግዜ ቢሰርዘው  ፫ግዜ “ድንግልበድንግልና ትፀንሳለች”የሚል ተጽፎ አነበበ።

    በመጨረሻም ሊቁ አረጋዊ ስምኦን የተጠራጠረውን ይህን “ድንግል በድንግልናትፀንሳለች” የሚለውን ቃል በዓይኑ ሳያይ እንደማይሞት መንፈስ ቅዱስ ገለፀለት።ስለዚህም ሉቃስ በወንጌሉ እንዲህ አለ፦ የጌታን መወለድ በዓይኑ ሳያይእንደማይሞት መንፈስ ቅዱስ ያደረበትና የገለጠለት ሰው ነበር [ሉቃስ 2.!6] 

    አረጋዊው ስምኦን እጅግ የተደነቀበትን ቃል ለ5)  ዓመታትያህል በተስፋ ጠበቀ፤እነሆ በዓይኑ የሚያይበት ግዜም ደረሰ፤ ይህም ጌታችን ከአንዲት የ05 አመት ታናሽገሊላዊት ብላቴና በህቱም ድንግልና በቤተልሔም በኤፍራታ መወለዱ ነው!!!

    ነቢዩ ኢሳያስ ስለ ፅዮን /ስለእመቤታችን/ ዝም አልልም እያለ በቤተልሔም ኤፍራታተገኘና የመላዕክቱን የእረኞቹን ዝማሬ ሰማና “ናሁ ድንግል ትፀንስ” እነሆ ድንግልበድንግልና ትፀንሳለች አለና የጌታን ልደት በዓይኑ ሊያይ ናፈቀና ትንቢቱ ከመፈፀሙከ7) ዓመታት በፊት አስቀድሞ  ተነበየ፤የዘመኑ ሰዎች አልታደሉምና እንዴት ድንግልበድንግልና ትፀንሳለች አሉና መጋዝ አመጡና ኢሳያስን ያዙና እነሆ ሥጋውን ለሁለትበመጋዝ ቆራረጡት!

    ነቢዩ ኢሳያስ የተነበየውን ትንቢት በዓይኑ አላየም። የኢሳያስን ትንቢት የተረጉመውአረጋዊ ስምኦን ግን በዓይኑ አየ፤ አንዳንድ ጊዜ እኛ ከምንናገረው ይልቅ ሰምተውየሚተረጉሙት የእግዚአብሔርን ቸርነት በዓይናቸው ያያሉ!

    አረጋዊ ስምኦን “ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች” የሚለውን ትንቢት ተረጎመበዓይኑም አየ አመነም! እንዲህም አለ ፦ “ዓይኖቼማዳኑን አይተዋልና ይገባዋልክብርና ምስጋና” ሉቃስ [2."]

    የክርስቶስን ልደት ስናነሣ ፈረንጆቹ ስለ ገና አባትና ስለ ገና ዛፍ ስለ በረዶ ያስባሉ።በአገራችንም ስለ ገና ጨዋታ ይታሰባል፡፡ በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናትም ገናየሕፃናት ነው ተብሎ ለሕፃናት ከረሜላ በማደል ይጠናቀቃል፡፡ የክርስቶስ ልደት ግንየመላው የሰው ዘር እንደገና የተወለደበት እንጂ ተራ የሕፃን በዓል አይደለም፡፡የልደትን በዓል ማክበር ብቻውን ክርስቲያን አያሰኝም፡፡ የእስልምና እምነት ተከታዮችየሆኑት የፍልስጤም አስተዳዳሪዎች የቀድሞ ያሲን አራፋት አሁን ደግሞ ማሕሙድአባስ በቤተ ልሔም ተገኝተው ያከብሩታል፡፡ የእኛ አከባበር ከዚህ የላቀ ካልሆነድካም ብቻ ነው፡፡ የተወለደውን ሕጻን በቁሳቁስ ሳይሆን በሕይወታችን ልናከብረው፤ደስታችንም በመብልና በመጠጥ ሳይሆን በፍቅሩ ሊሆን ይገባዋል፡፡

    ብዙዎች እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን እያሉ ይዘፍናሉ፣ ይጨፍራሉ፣ ይሰክራሉ፡፡ክርስቶስ ግን የተወለደው ዘፈን፣ ኃጢአትና ዝሙት ከተባሉት የጨለማ ሥራዎችሊያድነን መሆኑን ገና አላወቁም፡፡ ይልቁንም ቃሉ፡- “የእግዚአብሔርን የአምላክህንስም በከንቱ አትጥራ÷ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደልአያነጻውምና” ይላል (ዘፀ. !.7)፡፡ የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ማለትበስሙ በተሰየሙ ቀናት ኃጢአትን መሥራት ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔርንየኃጢአታችን ተባባሪ ማድረግ ነው፡፡ ፍርዱም ከፍ ያለ ነው።ይሁን እንጂየእግዚአብሔር ምህረቱ ሊነገር አይታሰብም ከቶም አይጀመርም። የዘመናት ጌታዘመኑ በተፈጸመ ጊዜ ከድንግል ተወልዶ “ዓመተ ምህረት” ሰጥቶናልና። እንደ ዓባይእንደ ጣና ባለ ባሕር ጽውዕ ምሉ ማር ጽውዕ ምሉ ቅቤ ቢጨምሩ ከመልኩከጣዕሙ እንደማይለውጠው ኹሉ የእኛም ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቸርነትአይለውጠውም።

    አንድም ወኃበ በዝንቱ ኃጢአት ህየ ፈድፈደት ጸጋሁ ለእግዚአብሔር እንዲልኃጢአት ከበዛች ዘንድ የእግዚአብሔር ጸጋ በዛች። ሮሜ [1.!3] እንዴት ቢሉበኃጢአቱ ቦታ ጽድቁ ስለገባ። አንድም ጌታ ሰው መኾኑ በምልአተ ኃጢአት ነውእንጂ በጥንተ አብሶ አይደለምና።/ከአዳምና ከሔዋን ዠምሮ በዘር የሚተላለፍኃጢአት ጥንተ አብሶ ይባላል/ በጥንተ አብሶ ሰው ኾኖ ቢኾን አዳምንና ሔዋንንብቻ ለማዳን ሰው ኾነ እንጂ እኛስ በመስዋዕታችን በግዝረታችን በጸሎታችን ዳንንባልን ነበር። ግዝረቱ መስዋዕቱ እንዳላዳነ ካሳየን በኋላ ከድንግል ተወልዶ ሰውኾነ።

    ኃጢአት ከበዛች ዘንድ የእግዚአብሔር ጸጋ በዛች! እንዲኽ ከኾነ የእግዚአብሔርጸጋ ይበዛልን ዘንድ ኃጢአት እንስራ እንላለንን?  አንልም።ቸርነቱን አድንቀን በንስሐእንመለሳለን እንጂ።

    የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መወለዱ የዓለምን ታሪክ ለሁለት የከፈለ ነው፡፡ ዛሬበክርስቶስ የሚያምነውም ሆነ የማያምነው ዓለም ዘመንን ሲቆጥር ከክርስቶስልደት በፊት ከክርስቶስ ልደት በኋላ እያለ ይቆጥራል፡፡ ለምን? ስንል ኢየሱስክርስቶስ የዓለምን ዘመን ለሁለት ስለከፈለው ነው፡፡ ከክርስቶስ ልደት በፊትየነበረው ዘመን ዓመተ ፍዳ፣ ዓመተ ኵነኔ ሲባል ከክርስቶስ ልደት በኋላ ያለው ዘመንግን ዓመተ ምሕረት ተብሏል፡፡ 

    ዲያቢሎስ በሥጋ ከይሲ ተሠውሮ ቢያስት ጌታችንም በሥጋ ብእሲ ሥግው ኾኖአዳነን! አምስት ሺህ አምስት መቶ ዓመት ሲፈጸም ከእመቤታችን ያላባት መወለዱቅድመ ዓለም ከአብ ያለናት መወለዱን ያስረዳል። ልደት ቀዳማዊ ተዓውቀበደኃራዊ ልደት እንዲል። ሰብአ ሰገል በኮከብ እየተመሩ ወደ ቤተልሔም መጡ።ኮከብ የተባለው የማታ ኮከብ ሳይኾን መልአክ ነው። እንዴት ታወቀ ቢሉ እነኾ ኮከብበማታ እንጂ በቀን አይታይም። ሰብአ ሰገልን ግን በቀን መራቸው። ኮከብ ወደምዕራብ ይሄዳል እንጂ ወደ ምስራቅ አይመራም። ሰብአ ሰገልን ግን ወደ ምስራቅመራቸው። ኮከብ ርቀት አለው ሰብአ ሰገልን ግን ከአናታቸው ጥቂት ከፍ ብሎመራቸው። ይህስ ኾኖ ለምን መልአኩ በኮከብ ተመሰላቸው ቢሉ ሰብአ ሰገልየኮከብ አጥኚ ወይንም አስትሮኖመርስ ስለነበሩ በለመዱት ነገር ለመሳብ ነው።

    “አውራ ጣቱን አሰረችው” 

    እመቤታችን ጌታን በወለደችው ጊዜ የጌታን አውራ ጣት አስራ ነበር። ምሥጢሩምን ይሆን ቢሉ እነሆ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንዲህ አድርገው ይገንዙሃል ስትል ነው።አንድም መንፈስ እንዳይደለ ለማሳየት ነው። መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምናአይታሰርም ነበር። አንድም በጨርቅ ጠቀለለችው። ይህም ምሥጢሩ አንድ ነው።(የዮሴፍና ኒቆዲሞስ መግነዝ ፣ መንፈስ አለመሆኑን ለማሳየት)

    ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ፦
    ዲያቆኑ በቅዳሴ ላይ ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ ይላል ፤ ሕዝቅኤል በትንቢቱ እንዲህአንዳለ፦ “በምሥራቅ የተዘጋ ጀጅ አየሁ; ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች እንጂአትከፈትም፤ ሰውም አይገባባትም ፤ የእስራኤል ቅዱስ ሳይከፍት ገብቶ ሳይከፍትወቶባታልና” ሕዝቅኤል #4.1
    ምሥራቅ እመቤታችን ናት ፤ መናፍቃኑ ግን ይህማ ስለቤተመቅደስ የተነገረ ነውይላሉ; ተዘግቶ የሚኖር ቤተመቅደስ አለ እንዴ? ሰውም የማይገባበት ቤተመቅደስየለም፤ ይህማ ስለእመቤታችን የተተነበየ ነው። ከምሥራቅ ፀሐይ እንደሚወጣከምስራቋ እመቤታችን ፀሐይ ጌታ ተወልዷልና። አንድም ይህች በር ተዘግታትኖራለች እንጂ አትከፈትም አለ; ድንግል በክልኤት ናትና; በሥጋም በነፍስምድንግል ናትና ፤ ቅድመ ፀኒስ ወሊድ ድንግል ፤ ጊዜ ፀኒስ ወሊድ ድንግል ፤ ድህረፀኒስ ወሊድ ድንግል ናትና; ወትረ ጊዜ ድንግል ናትና ሲል ነው። አንድም “ሰውምአይገባባትም” አለ አንድያ ልጇን ብቻ ወልዳለችና። የእመቤታችን ክብርማ መቼተነገረና? የእመቤታችን ፍቅርማ መቼ ተነግሮ ይፈጸምና? ስለፍቅሯ ለመዘመርለመቃኘት…ሞከሩ ግን መቼ የእናቴ ፍቅር በቀላሉ ይነገርና? መቼ እንዲህ በቀላሉ? 

    “ይህች ለዘለዓለም ማረፊያዬ ናት”

    እግዚአብሔር ፅዮንን መርጧታልና፤ ዛቲ ይዕቲ ምዕራፍየ ለዓለም (ይህችለዘለዓለም ማረፊያዬ ናት) መርጫታለሁና በእርሷም አድራለሁ። መዝ )"1.03
    ሐዋርያው ዮሐንስ “ቃልም ሥጋ ሆነ” እንዳለ ጌታችን ከእመቤታችን ሥጋን ነስቶተወለደልን። ከእመቤታችን የነሳው ያ ቅዱስ ሥጋ ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ ብሎ ዐረገ።ክርስቲያን ሆይ ከእመቤታችን የተነሳው ያ ቅዱስ ሥጋ ወደሰማይ ዐርጓል እንጂበምድር ተቀብሮ በስብሶ የቀረ እንዳይመስልህ። ይህች ለዘለዓለም ማረፊያዬ ናትእንዲል።

    ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ አለ፦

    በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፤ ቃልም እግዚአብሔርነበረ … “ቃልም ሥጋ ሆነ” [ዮሐ 1.1]

    በመጀመሪያ ቃል ነበረ፦ “በመጀመሪያ” የሚለው ቃል “በመጀመሪያ” እግዚአብሔርሰማይንና ምድርን ፈጠረ ከሚለው ይለያል፤ [ዘፍ1.1] ሰማይና ምድር ለመፈጠርየተወሰነ ጊዜ ነበራቸው፤ በመጀመሪያ ቃል ነበረ የሚለው ግን በሰውኛ አገላለፅእንዲገባን ነው እንጂ የተወሰነ ጊዜን አያመለክትም። ቁጥር እንኳን መጀመሪያናመጨረሻ የለውም፤ ቃል [ወልድ ዋህድ ኢየሱስ ክርስቶስም] የመጀመሪያው አልፋየመጨረሻው ዖሜጋ ነው። ራዕ !2
    በመጀመሪያ ቃል ነበረ አዎ ያም ቃል እግዚአብሔር ነበረ! ሥጋንም ለበሰ፤ ከማን?ከማን ሥጋን ነሳ? ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ በኤፍራታበቤተልሔም ተወለደ!! ልበአምላክ ዳዊት ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ መዝ. [131:6]እነሆ በኤፍራታ ሰማነው እንዳለ ከሀገር ለይቶ በቤተልሔም ከቦታ ለይቶ በከብቶችግርግም ከሴቶች ለይቶ ከእመቤታችን ተወለደ። ህጻን ተወልዶልናል ወንድ ልጅምተሰቶናል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙ ድንቅ መካር ኃያል አምላክየዘላለም አባት የሠላም አለቃ ተብሎ ይጠራል። ኢሳይያስ 9.6
    እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን!

    ***//***

    የጌታችን ልደት መልእክት!

    አንዱ ሸረፌ የሚባል ባለጸጋ ነበር። ሹሙን ጠርቶ በቀን በቀን ፩ድ ወቄት ዱቄትለድኾች ሳትሰጥ አትዋል አለው። ቢሰጥ እየበዛ ሔደ። ከበዛስ ብሎ ከታዘዘውአብልጦ ፪ ወቄት ዱቄት ይሰጥ ዠመር። ባለጸጋው ከቤተ መዛግብቱ ቢገባንብብረቱ በዝቶ አገኘው። ሹሙንም ያዘዝኹህን ትተሃል እንዴ? ሲል ጠየቀው።ሹሙም እንዲያውም አብልጬ እሰጣለሁ አለው። እንግዲያው አትገምግም እጅህእንዳነሳ ስጥ ብሎታል።

    የተቸገረ ብታይ ከንፈር ከመምጠጥ የቻልካትን ትንሿን አድርግለት! ሐዋርያውበሥራና በምግባር እንጂ በቃል ብቻ አንዋደድ እንዲል ለድኾች የቻልነውን እንስጥ!በየበአላቱ ዶሮ በማይጮኽበት ጢስ በማይጤስበት ቤት ያለችንን ተካፍለንእንብላ! ትዝ ይለኛል ልጅ እያለኹ እንደ ልደተ ክርስቶስ ባሉ በዓላት ላይ ከክፍልጓደኞቼ ጋር ዶሮ እያሰራን ለድኾች እናበላ ነበር።

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: “ቃልም ሥጋ ሆነ” [ ዮሐ 1-1 ] Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top