• በቅርብ የተጻፉ

    Monday 9 November 2015

    የብሕትውና(የምንኩስና) ኑሮ - ክፍል 3


    ምንኵስና በኢትዮጵያ

    4ኛው // በፊት

    ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ሀገራችን የገባውበኢትዮጵያ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽበአባ ጳኩሚስ ዘመን ቢሆንም የብሕትውና ኑሮ ግንበሀገራችን ከዚያም ቀድሞ እንደነበረ የሚጠቁሙአንዳንድ መረጃዎች አሉ፡፡

    አባ አሞንዮስ፡- ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ኢትዮጵያከመግባቱ በፊት አሞንዮስ የተባሉ ባሕታዊ በተንቤንቆላ ደብረ አንሣ በተባለው በረሃ በጾም በጸሎትተወስነው ይኖሩ ነበር፡፡

    አባ ዮሐኒ፡- በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መግቢያላይ በትግራይ ተንቤን አውራጃ በሀገረ ሰላም ቀበሌተወለዱ፡፡ በዚያን ዘመን ሥርዓተ ምንኵስና ወደኢትዮጵያ ባይገባም አበው በምናኔ በበረሃ ይኖሩነበር፡፡ የአባ ዮሐኒ ቤተሰቦች ድሆች ስለነበሩ አባአሞንዮስ ወስደው አሳደጓቸው፡፡ ካደጉ በኋላምከአባ አሞንዮስ ተለይተው ወደ በረሃ ለብቻቸውበመውረድ በተጋድሎ ሲኖሩ ከቆዩ በኋላ በተወለዱበ3ዐ ዓመታቸው ኀዳር 5 ቀን እግዚአብሔር ወደብሔረ ሕያዋን በመላእክት እጅ እንደወሰዳቸውገድለ አባ ዮሐኒ ይገልጣል፡፡

        ሥርዓተ ምንኵስና በኢትዮጵያ ለመስፋፋትየበቃው በሁለት ዓይነት መንገድ ነው፡፡

    ከውጭ ወደ ሀገራችን በገቡ ቅዱሳን

    በኢትዮጵያውያን ቅዱሳን

    ወደ ሀገራችን የገቡ ቅዱሳን፡

    ከመካከለኛው ምሥራቅ፣ ከታናሸ እስያና ከሮማግዛት ወደ ሀገራችን በልዩ ልዩ ምክንያት ገብተውሥርዓተ ምንኵስናን ያስፋፉ ገዳማትን የገደሙአበው አያሌ ሲሆኑ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉትናቸው፡፡

    አባ ሊባኖስ፡-

    በቁስጥንጥንያ አጠገብ ሩም በተባለች ቀበሌተወለደ፡፡ በልጅነቱ በዲቁና ሲያገለግል ቆይቶ ወደግብፅ በመምጣት ሥርዓተ ምንኵስና ተፈጸመለት፡፡ወደ እስክንድርያ በመጓዝም እስከ ቁምስና ማዕረግየደረሰ አባት ነው፡፡ በ486 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያበመምጣት 8ዐ ዋሻዎች አንፆ ሥርዓተ ምንኵስናንአስፋፍቶ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥትጥር 3 ዐርፏል፡፡

    ተስዐቱ ቅዱሳን

    ተስዐቱ ቅዱሳን

    ተሰዐቱ ቅዱሳንበኬልቄዶን ጉባዔ የልዮን ጦማር ያልተስማሙትንኦርቶዶክሳውያን አባቶች ሮማውያን በግፍበሚያሳድዱበት ዘመን ከሮም፣ ከታናሽ እስያናከመካከለኛው ምሥራቅ ወደ ግብፅ በመውረድበዚያም ሥርዓተ ምንኵስናን ፈጽመው፣ ተምረው፣በአንድነት በ48ዐ ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ በመምጣትሥርዓተ ምንኵስናን የበለጠ ያስፋፉ አበው ናቸው፡፡ገዳማቱ እስከዛሬ ድረስ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ዘጠኝቅዱሳንም የሚከተሉት ናቸው፡፡


    አቡነ ዮሐንስ (ዘጎንድ ተ/ሃይማኖትአቡነ ዮሐንስ (ዘጐንድተ/ሃይማኖት)

    የትውልድ ሀገራቸው ፍልስጥኤም ሲሆን ወደኢትዮጵያ የገቡት በ11ዐዐ ዓ.ም. ነው፡፡ አባ ዮሐንስበተለይ ከአፋር ክልል ደብረ አዘሎ፣ ደብረ ደንኖ፣ደብረ ፀገ፣ ደብረ ገሮ፣ ደብረ አሳራ በተባሉሥፍራዎች ሥርዓተ ምንኵስናን አስፋፍተዋል፡፡በመጨረሻም በለሳ በረሃ ወርደው ጐንድ ገዳምንበመመሥረት ሐምሌ 29 ቀን በተወለዱ በ5ዐዐዓመታቸው በ15ዐዐ ዓ.ም. ዐርፈዋል፡፡

    ጻድቃን

    ተሰዐቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸውበፊት በግልና በኀብረት እየሆኑ አያሌ መነኰሳትወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ገብተው ነበር፡፡እነዚህም ቅዱሳን (ጻድቃን) እየተባሉ ሲሆን በቅርቡመጽሐፈ ገድላቸው እስከ ተገኘበት ጊዜ ድረስስለነርሱ የሚታወቀው እጅግ ጥቂት ነበር፡፡እነርሱም በኤርትራ ቆላማው ሥፍራ ሥርዓተምንኵስናን ያስፋፉ መሆናቸው ታውቋል፡፡

    አርባ ሐራ፡-

    አቡነ ሐራ የተባሉት ቅዱስ በዘጠነኛው መቶ ክፍለዘመን ከግብፅ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት በአኵስምከቆዩ በኋላ አያሌ መጻሕፍት እና ንዋያተ ቅድሳትይዘው ወደ መንዝ ማማ ምድር በመምጣት በዋሻውስጥ ተቀመጡ፡፡ የዮዲት ዘመን ካለፈ በኋላደግሞ 4ዐ ቅዱሳን ከግብፅ ከገዳመ አስቄጥስመጥተው ከአቡነ ሐራ ጋር 4 ሰዓት የሚያስኬድ ዋሻፈልፍለው ማኀበረ መነኰሳት አቁመው መኖርጀመሩ፡፡

    ከዚህም መካከል 2ዐዎቹ ዞረው ሲያስተምሩ2ዐዎቹ ደግሞ የተግባር ቤቱን ሥራ ያከናወኑ ነበር፡፡

    በአካባቢውም ትምህርተ ወንጌልንና ሥርዓተምንኵስናን ካስፋፉ በኋላ አስቀድመው 4ዐውቅዱሳን በኋላም አቡነ ሐራ በተወለዱ በ22ዐዓመታቸው በ11ዐዐ ዓ/ም ዐረፉ፡፡ የእርሳቸውንምፈለግ አባ ፍሬ ሠናይ የተባሉ አባት ተከተሏቸው፡፡ይህም ሥፍራ ዛሬ አርባራ መድኃኔዓለም ገዳምበመባል ይታወቃል፡:

    በአሁኑ ወቅት ይህ ቦታ በተለያየ አፅፍ የተከፈኑ እናየተገነዙበትምማሠሪያ ክር በእጃቸውናበእግራቸውጣት ላይ የሚታይ ብዙ አፅሞች ይገኙበታል፡፡ምንም እንኳን ዋሻው በአፅም የተሞላ ቢሆንምከአካባቢው የሚወጣው መዓዛ ግን ከሙታንመንደር የሚገኝ መጥፎ ሽታ ሳይሆን (አልባብአልባባ) የሚል መልካም መዓዛ ነው፡፡

    የአካባቢው አረጋውያን እንደሚናገሩት ከሆነከኢጣሊያ ፋሺስት ወረራ በፊት ዘወትርየማኀሌት÷የከበሮና የዕልልታ ድምፅ ይሰማበትነበረ፡፡ በተጨማሪም እጅግ ግዙፍ የሆነ ነጭ አሞራእየበረረ ወደ ዋሻው ሲገባ ማየት የዘወትር ክስተትነበረ፡፡ ከዚያ ወዲህ ግን ይህ ነገር ብዙምአይታይም፡፡

    ቦታውን ከአካባቢው ምእመናን ጋር የሚያገናኘውሌላው ነገር ደግሞ መሬት ሰብል እንዳትሰጥ ሰብልአጥፊ ተባይ ሲነሣ፣ እንስሳቱ ወተት መስጠታቸውንሲቀንሱ ገበሬዎቹ አፅሞቹ ካረፉበት ቦታ አፈሩንበመዝገን በማሳቸው ላይ ይበትናሉ፤ እንስሳቱንምያሻሹበታል፡፡ እንደ እምነታቸውምእንደሚያደርግላቸው በየዓመቱ ጥር 13 ቀንየሚገባው የእንስሳትና የሰብል ውጤት ምሥክርነው፡፡ ከዋሻው የሚወጣው መልካም መዓዛምአሁንም ያልተቀየረ መሆኑን ሄዶ የሚመለከትምሥክር ነው፡፡

    አባ ኖብ

    ትውልዳቸው በሶሪያ ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ወጥተውከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ጋር ተገናኙ፡፡የኢትዮጵያውያንን ቋንቋና ባሕል ካጠኑ በኋላበትግራይ ተንቤን ፀፀራ ወረዳ ከሚገኘው ዋሻ ላይቤተ ክርስቲያን ተክለው ገዳም መሠረቱ፡፡ ከዚያምቀጥለው በመላ ኢትዮጵያ በመዘዋወር ገዳማትንመሥርተው በ11ዐዐ ዓ.ም. ኀዳር 8 ቀን ዐረፉ፡፡

    አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

    አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስትውልዳቸው በግብፅ ሲሆን ገና በሕፃንነታቸውበልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ በ11ዐዐ ዓ.ም. ወደኢትዮጵያ በመምጣት ሥርዓተ ምንኵስናን ያስፋፉአባት ናቸው፡፡ እግዚአብሔር በሰጣቸው የ562ዓመት ዕድሜ አያሌ ገዳማትን የገደሙ ሲሆንበተለይም የዝቋላና የምድረ ከብድ ገዳማትእስከዛሬ የፀኑ ናቸው፡፡

    በኢትዮጵያ የምንኵስናና የገዳማት ታሪክ ውስጥከ3ኛው - 12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ያለው ጊዜበአብዛኛው ከውጭ በመጡ አበው ሥርዓተምንኵስና የተስፋፋበት ሲሆን ከ12ኛው-15ኛውያለው ደግሞ ከመላ ኢትዮጵያ በተነሡ አበውቅዱሳን ሥርዓተ ምንኵስናና የገዳማት ትክልከሰሜን ወደ ምዕራብ፣ ምሥራቅና ደቡብየተስፋፋበት ወቅት ነው፡፡



    ዋቢ

    1.    ትንሣኤ ቁ.99/1978

    2.    ገድለ አባ ሊባኖስ

    3.    ገድለ አባ ዮሐንስ

    4.    ዜና መንዝ

    5.    የአንኰበር መሳፍንት የታሪክ መጽሐፍ

    6.    ትንሣኤ ቁ.11/79

    7.    ትንሣኤ ቁ.22/80

    8.    Conti Rossini, steria PL.XLIV

    9.    ሉሌ መላኩ፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ አ.አ1986

    10. አባ ጎርጎርዮስ፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለምመድረክ

    11. አባ ጎርጎርዮስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንታሪክ

    ሐመር መጽሔት

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: የብሕትውና(የምንኩስና) ኑሮ - ክፍል 3 Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top