• በቅርብ የተጻፉ

    Monday 16 November 2015

    በእንተ ማርያም

    ድንግል ማርያም ከምድራውያን ሰዎችየተወለደች፤ ለሰማያዊ ንጉሥ እናት የሆነች፤በሰማያውያን ሥርዓት /በቅድስና ባጌጠ ኑሮ/የኖረች፤ ከከበሩት የከበረች ሴት ናት፡፡ “እመቤታችንቅድስት ድንግል ማርያም ከዳዊት ከአብርሃም ዘርተወለደች” /ሃይማኖተ አበው ገጽ 577/፡፡ ወልድሥጋ እና ነፍስ የነሣው ከአብርሃም ዘር /ከማርያም/እንደሆነ የታመነ ነው፡፡ ዕብ. 2፡16፡፡ “ጌታችንባሕርያችንን ባሕርዩ ለማድረግ ነውር ነቀፋከሌለባት ድንግል ባሕርያችንን ወሰደ፡፡” /ቅዱስአትናቴዎስ/፡፡

       ከሐና እና ከኢያቄም በሕግ በሆነ ሩካቤተወለደች፡፡ “ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወትየተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ፡፡” /ቅዳሴ ማርያም ቁ. 38/፡፡ በመቅደስ ቃሉን እየሰማችና እያገለገለችበንፅሕና አደገች፡፡ “በዋዛ ፈዛዛ ያደግሽ አይደለም፡፡በንጽሕና በቅድስና በቤተመቅደስ እንጂ፡፡” /ቅዳሴማርያም ቁ. 39/፡፡

       እግዚአብሔር ወዳሰበላት ዓላማ መራት፡፡ የልጁዙፋን ሊያደርጋት ወስኗልና፡፡ በጸጋው ዙፋን ፊትለፊት በቅድስና እያስጌጠ አሳደጋት፡፡ ልጁማደሪያው አደረጋት፡፡ መንፈሱ በጽድቅ አገዛት፡፡“አንቺን የወደደ እግዚአብሔር አብ ቅዱስ ነው፡፡በማህፀንሽ ያደረ ወልድ ዋህድ ቅዱስ ነው፡፡ ያጸናሽየጽድቅ መንፈስ ጰራቅሊጦስም ቅዱስ ነው፡፡” /ቅዳሴ ማርያም ቁ. 26/፡፡

       የእግዚአብሔር ማዳን የሚገለጥበት ጊዜ ደረሰ፡፡ከዙፋኑ ትእዛዝ ወጣ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ይህንትእዛዝ ይዞ ወደ ድንግሊቱ በረረ፡፡ ሉቃ. 1፡27፡፡ ብርሃናዊ መልአክ ከብርሃን ፍጥነት በላይ ፈጠነ፤የያዘው ለትውልድ ሁሉ የዘመናት ጥያቄ መልስነ ውና፤ ሰው የሚድንበት የአምላክን እቅድ ይዟልና፡፡ ቅዱስ ዲዮናስዮስ “ገብርኤል የመላውን ዓለምድኅነት ያበስር ዘንድ እየበረረ መጣ፡፡ ገብርኤልየሴት ጾታ ከውድቀት ወደ ክብር መሸጋገሩን ያውጅዘንድ ወደ ድንግል ተላከ፡፡” በማለት መስክሯል፡፡

      መልአኩ ድንግሊቱን “ደስተኛይቱ ሆይ ደስይበልሽ፣ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ጌታ ከአንቺ ጋር ነውና፡፡አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ” አላት፡፡ ሉቃ. 1፡28፡፡ ሰላምታው ውበቷን ያበራል፤ ብልጫዋንያውጃል፡፡ ሰላምታው ሰላምታ ብቻ አልነበረም፤የመለኮትን አላማ፤ የሰውን ዘር ብስራት /የድኅነትዜና/ ቋጥሯልና፡፡ ድንግሊቱ “ይህ እንዴት ያለሰላምታ ነው?” ብላ አሰበች፡፡ እውነት ነው!የሚያሳስብ፤ የሚያስደንቅ ሰላምታ ነው፡፡ የዘልማድሰላምታ አልነበረምና፡፡ ሉቃ. 1፡30፡፡ መልአኩ“በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝተሻልና አትፍሪ፡፡እነሆ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ ስሙንምኢየሱስ ትይዋለሽ” አላት፡፡ ሉቃ. 1፡31፡፡ ይህመርዶን የገለበጠ ብስራት /የነፃነት ዜና/ ነው፡፡ ይህየነፍስን ትካዜ የሚነቅል ዜና ነው፡፡ ድንግል ማርያምያመነች ቤተክርስቲያንን ወክላ ይህን የማዳን ዜናሰማች፡፡ ድንግል ማርያም የዓለም መድኃኒት ወደዓለም የገባባት በር ናት፡፡ ድንግል ማርያምየቤተክርስቲያን አንደበቷ ነበረች፡፡ እንዳለ ቅዱስያዕቆብ ዘስሩግ፡፡

       ታላቁ አዳኝ /saviour/ የሚወለደው ከእርሷ ያለአባት እንደሆነ ሰማያዊው አረጋገጠላት፡፡ እርሷም“ወንድ ስለማላውቅ እንዴት ይሆናል?” አለች፡፡ ሉቃ. 1፡34፡፡ መልአኩ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ በድንግልናእንደምትወልድ ነገራት፡፡ የዘመዷ የኤልሳቤጥንበስተርጅናዋ መፅነስ ዋቢ አድርጎ አቀረበላት፡፡ ነገርግን ኤልሳቤጥ ብታረጅም ባል ነበራት፡፡ በካህኑ ቤት ለመስራት እርጅና አላገደውም፤ ማርያም በድንግልናእንድትወልድ ሲሰራ አልተሳነውም፡፡ መልአኩ“ለእግዚአብሔር የሚሳነው የለም” አላት፡፡ ይህንግግር የክርክር ፍፃሜ፤ የእምነት መጀመሪያ ነው፡፡ድንግልም “እንደቃልህ ይሁንልኝ” ብላ በእምነትታዘዘች፡፡ በመቻሉ ተደገፈች፡፡ እንደቃሉ ሁሉም ሆነ፡፡አዳኙ /መሲሁ/ በሥጋ ተገለጠ፡፡ ከዚህ የተነሣማርያምን እንወዳታለን፡፡ “ማርያም ሆይ ስለዚህእንወድሻለን፤ ከፍ ከፍም እናደርግሻለን፤ እውነተኛየጽድቅ መብልንና የሕይወት መጠጥንወልደሽልናልና፡፡” /ቅዳሴ ማርያም ቁ. 9፤90/፡፡አዳምን ከውድቀት የሚያነሣውን ስለወለደችእንወዳታለን፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም “የተሰደደውን አዳምየሚመልሰው የሕይወት ዛፍ የተገኘው ከእርሷነው፡፡” እንዳለ፡፡ እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይበእውነት ምስጋና ይገባሻል፡፡ የእግዚአብሔር እናቱሆነሻልና፡፡ በእውነት መደነቅ ይገባሻል፡፡ ዓለምንሁሉ በመሀል እጁ የያዘ እርሱን ወልደሻልና፡፡በእውነት ብፅዕና ይገባሻል፡፡ ለእውነተኛ ፀሐይመውጫ ሆነሻልና፡፡ በእውነት መመስገን ይገባሻል፤ለማለዳው ኮከብ ምስራቅ ሆነሻልና፡፡” /አባጊዮርጊስ ዘጋስጫ/፡፡ “የአምላክ እናት የማያቋርጥደስታ መፍሰሻ ድንግልሆይ በድጋሜ ምስጋናአቀርብልሻለሁ፡፡” አባ ማቶዲዮስ፡፡

       እውነት ነው! የዳዊት መክፈቻ ላለው ንጉሥ ዙፋንሆናለችና ክብር ይገባታል፡፡ ልጇ ክብሯ፣ ደስታዋ፣የመንፈሷ ከፍታና የሕይወቷ ጌታ ነው፡፡ድንግልማርያምን ለመውደድና ለማክበር አምላክንመውለዷ ከበቂ በላይ የሆነ አመክንዮ ነው፡፡

    ኢየሱስን መውደድ ማርያምን በመጥላት አይገለፅም፡፡ ኢየሱስን መውደድ እርሱ ያከበራቸውን በማቃለል አይገለፅም፡፡ ኢየሱስን የሚወዱ ጠላቶቻቸውን እንኳ ወደ መውደድ ያድጋሉ እንጂ የጌታን ወዳጆች አይጠሉም፡፡  ድንግል ማርያም መንፈስ ቅዱስ ስሟን በደስታ የሚጠራውን ትውልድ አሳያት፤ እንዲህም አለች “እነሆ ከዛሬጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፡፡ ” ሉቃ. 1፡48፡፡ አንቺን የተጠጋ እምነቱንም በልጅሽ ያደረገ የተመሰገነ ነው፡፡ የፍቅርሽ መሰረት ከልቦናውየማይነዋወጥ የተደነቀ ነው፡፡ ዘወትር ለምስጋናሽየሚተጋ የተመሰገነ ነው፡፡ የልጅሽን የሞቱን መስቀልለመሸከም ዘወትር ልቡን የሚያስጨክን የተመሰገነነው፡፡ ከልጅሽ የመገዛት ቀንበር በታች ራሱን ዘንበልያደረገ የአንድ ልጅሽን የወንጌሉን ፍለጋ የተከተለየተመሰገነ ነው፡፡ እግዚአብሔርን የሚፈሩበመንገዱም የሚሄዱ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፡፡ድንግል ሆይ በጸሎትሽ ረዳትነት የሚታመን ምስጉንነው፡፡ እኔም ስለዚህ ፍቅርሽን ለመከተል ተጋሁ፡፡” /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ/

    ድንግል ማርያም፡-

    የአምላክ እናት ናት፡በጉባኤ ኤፌሶንድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ መሆኗተገልጦአል፡፡ “ማርያም ወላዲተ አምላክ /ቴዎቶኮስ/ ተብላ መጠራት አለባት ተብሎበጉባኤው ድምፅና ፍላጎት ተወሰነ፡፡” ዝኒከማሁ፡፡ ኤልሳቤጥም በመንፈስ ቅዱስተሞልታ “የጌታዬ እናት” ብላ መስክራለችና፡፡ሉቃ. 1፡43እናታችን ናት፡- ማርያም በሥጋ ከኢየሱስሌላ ልጅ የላትም፤ እርሱንም በድንግልናወለደች፡፡ በመንፈስ ስንረዳ ግን ማርያምመንፈሳዊት እናታችን ናት፡፡ ጌታ ለዮሐንስ“እናትህ እነኋት” ብሎ እናቱን ለወዳጁ ሰጠ፡፡ ዮሐ 19፡26-28፡፡ ዮሐንስ በሥጋየወለደችው እናት ስላለችው ተጨማሪ እናትአታስፈልገውም፡፡ ኢየሱስ አደራ መስጠትከፈለገ ደግሞ “እናቴን አደራ” ማለትነበረበት እንጂ “እናትህ እነኋት” አይልምነበር፡፡ ስለዚህ ለዳነው ትውልድ እናቱን እናትአድርጎ መስጠቱን ያሳያል፡፡ 

    ሔዋን የሰውዘር ሁሉ እናት ናት፡፡ ድንግል ማርያም ደግሞየዳነው ትውልድ ሁሉ እናት ናት፡፡አምብሮስ፡፡እመቤታችን ናት፡- ድንግል ማርያም የንጉሡ እናት፤ የእኛም እመቤት ናት፡፡

    ምሳሌያችን ናት፡- የክርስቲያኖች ፀሐፊአምብሮስ “ከእመቤታችን ምን ያህልየደግነት አይነቶች አንፀባርቀው ወጥተዋል፡፡እርሷ የውብ ክርስቲያናዊ ሕይወት ምሳሌናት፡፡” በማለት የድንግልን ምሳሌነትገልጧል፡፡ የድንግል ስሟ ብቻ ሳይሆንሕይወቷም ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለ ድንግልመናገራችን መልካም ነው፤ ምሳሌያችን አድርገናት የሚነገርለት/ 

    የሚናገር ሕይወት የሚኖረን መቼ ነው?  ክርስትናችን ከፊደል ወጥቶ በመንፈስ፤  ከንግግር አልፎ በኑሮ የሚገለጠው መቼ ነው? ድንግልን በብዙ ምሳሌ መስለናታል፤ ነገር ግን በሕይወት አልመሰልናትም፡፡ ከድንግል የሕይወት ገጽየሚያንጸባርቁ መልካምነቶች አሉ፡፡ እርሷየክርስትና ትልቅ ፊደል ናት፡፡

    አማላጃችን ናት፡- መጽሐፍ ቅዱስበመዘገበው በቃናው ሰርግ የድንግልማርያም ምልጃ ተገልጧል፡፡ ይህ የድንግልምልጃ በልጇ ሁሉን ቻይነት መተማመኗንያሳያል፡፡ በምልጃዋም ዶኪማስ ከመዋረድዳነ፤ የልጇ የኢየሱስ ክብር ለዓለምተገለጠ፡፡ ድንግል ማርያም አሁንም

    በቀደመልመናዋ (ውዳሴ ወቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ተመልከት) መዳኑ ያላቸው ከመዳንእውቀት እንዳይንሸራተቱ፤ መዳንንያልተቀበሉ ደግሞ በልጇ አምነውበእግዚአብሔር ጽድቅ እንዲቆሙታማልዳለች (በጸሎትዋ ታግዛለች)፡፡“ሴቲቱጠበቃዋን በሴት አገኘች፡፡” ቅዱስ ጎርጎርዮስዘኑሲስ፡፡ “ቅድስት ሆይ ለምኝልን” ቅዱስኤፍሬም፡፡

    ክሌይስ /ለተዘጋብን መክፈቻ/ በሚል ርእስ በዲ/ን ጋሻው ዘመነ ከተጻፈ መጽሐፍ ተወሰደ፡፡

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: በእንተ ማርያም Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top