• በቅርብ የተጻፉ

    Monday 16 November 2015

    ዘመነ ጽጌ


    «ድንግል ሆይ ርጉም በሆነ ሄሮድስ ዘመንከልጅሽ ጋር ከሀገር ሀገር ስትሸሺ ከአንቺ ጋርመሰደዱን አሳስቢ ፤
    ድንግል ሆይ ከዓይንሸ የፈሰሰውንና በተወደደልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባአሳስቢ፤ ድንግል ሆይ ረሐቡንና ጥሙን፣ችግሩንና ሐዘኑን፣ ከእርሱ ጋር የደረሰብሽንምጭንቅ ሁሉ አሳስቢ››

    ቅዳሴ ማርያም

    ጽጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን ዘመነጽጌ ማለት የአበባ ዘመን ማለት ነው፡፡በሀገራችን መስከረም 25 ቀን ዘመነክረምት አልፎ መስከረም 26 ቀን ዘመነጽጌ ይጀምራል፡፡ ዘመኑ አበቦችየሚያብቡበትና ሜዳዎችንና ተራሮችንየሚያስጌጡበት ዘመን ነው፡፡ ፍሬ የተባለጌታን ያስገኘች እመቤታችን በአበባትመሰላለችና ዘመኑ የጌታንናየእመቤታችንን ነገር በአበባና በፍሬለመመሰል የተመቸ ነው፡፡ስለዚህምየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶቤተክርስቲያን ከመስከረም 26 ቀን ጀምሮእስከ ኅዳር 6 ቀን ድረስ የጌታን እናየእመቤታችን ስደት ታስባለች፡፡

    በዚህ ዘመን ቅዱስ ያሬድ እና አባ ጽጌድንግል ባዘጋጇቸው ድርሰቶች የጌታችን እናየእመቤታችን ስደት በማኅሌት ይታሰባል፤ምስጋና እና ልመና ይቀርባል። ምእመናንቤተክርስቲያናቸው በሠራችላቸው ሥርዓትመሠረት በፍቅርና በደስታ ይዘክሩታል ፡፡ከዚህም በተጨማሪ ስደቱን ለማሰብናበረከት ለማግኘት በርካታ ክርስቲያኖችየአዋጅ ጾም ባይሆንም በፈቃደኝነት ዘመኑንበጾም ያሳልፉታል፡፡

    የእመቤታችን ስደት የመጀመሪያውየአዲስ ኪዳን ስደት ነው፡፡ ከገነትየተሰደደውን አዳምን ወደ ቀደመ ክብሩናመንበሩ ከዚያም ወደ ሚበልጥ ክብርለመመለስ የተወለደው ጌታችንናአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ገና ከህፃንንቱጀምሮ ስደትን እና መከራን ተቀብሏል፡፡ወንጌላዊው ማቴዎስ እንደጻፈው፤ ጌታችንመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስበተወለደበት ጊዜ ሰብአ ሰገል «የተወለደውየአይሁድ ንጉሥ ወዴት አለ? በምሥራቅኮከቡን አይተን ልንስግድለት መጥተናል»እያሉ በኮከብ እየተመሩ በመጡ ጊዜበይሁዳ፣ በገሊላና በሰማርያ የሮማውያንተወካይ የነበረው ንጉሥ ሄሮድስ የጌታችንንግሥና ምድራዊ ንግሥና መስሎትመንግስቴን ሊቀማኝ ነው ብሎ ደነገጠ፡፡ፊሪሳውያን «መሲህ ተወልዶ ከሮማውያንአገዛዝ ነጻ ያወጣናል፡፡» ብለው ያምኑእንደነበር ስለሚያውቅም ይህ የተፈጸመመስሎት ጭንቀቱ በረታ፡፡ የተወለደውንሕፃንም ለመግደል ተነሳ፡፡

            ስለዚህም ሰብአ ሰገልን አስጠርቶ«ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ፤ ባገኛችሁትም ጊዜእኔም እንድሰግድለት ወደ እኔ ተመልሳችሁያለበትን ንገሩኝ» በማለት በሽንገላተናገራቸው፡፡ጠቢባኑም ከሄሮድስ ከተለዩበኋላ በኮከቡ እየተመሩ ጉዞአቸውንቀጥለው ጌታችንን ከእናቱ ጋር አገኙት ፤ተንበርክከው ሰገዱለት፤ ወርቅ ፣ ዕጣን፣ከርቤ እጅ መንሻ አቀረቡለት፡፡የእግዚአብሔር መልአክ ወደ ሄሮድስእንዳይመለሱ፤ ነገር ግን መንገድ ቀይረውወደ ሀገራቸው እንዲሄዱ በነገራቸውመሠረት በሌላ መንገድ ወደ መጡበትተደብቀው ተመለሱ፡፡ሄሮድስም ሰብአ ሰገልእንደተሳለቁበት ባወቀ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ/ጌታን ለማስገደል በማሰብ /በአማካሪዎቹግፊት  ጌታ በተወለደባት ከተማበቤተልሔምና በአውራጃዋ የነበሩትንከአንድ ዓመት ተኩል እስከ ሁለት ዓመትየሚሆን ዕድሜ ያላቸውን ሕጻናትንአስገደለ፡፡ /ማቴ. 1.13-18

    «እነርሱም(ሰብአ ሰገል ) ከሄዱበኋላ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍታይቶ «ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለውይፈልገዋልና ተነስ፤ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህወደ ግብጽ ሽሸ፤ እስክነግርህም በዚያተቀመጥ አለው፡፡ » /ማቴ. 2 13  14/እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊትያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ ልጄን ከግብጽጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብጽሔደ፡፡ ሄሮድስ እስኪሞት ድረስም በዚያኖረ፡፡ /ማቴ 2-13-15/ ተብሎ እንደተጻፈሁሉ፤ ዮሴፍም ተነሣ፤ በዕድሜዋ በጣምልጅ የነበረችው እመቤታችን ገናየተወለደውን ሕፃን አቅፋ የምትቀመጥበትአህያም ተዘጋጀ፡፡ ጉዞአቸውን ጀመሩ፡፡ከእስራኤል ወደ ግብጽ በእግር ለመሔድየሲናን በረሃ ማለፍ የግድ ነው፡፡ በዚያንዘመን ከእስራኤል ወደ ግብጽ የሚወስዱሦስት የተለያዩ መንገዶች ነበሩ፡፡ በሽፍቶችላለመጠቃት መንገደኞች በቡድን በቡድንሆነው በእነዚህ መንገዶች ይሔዱ ነበር፡፡

    እነርሱ ግን ንጉሥ ሔሮድስተከታትሎ ሊይዛቸው ስለሚችል በእነዚህመንገዶች መሔድ እንደሌለባቸው ግልጽነው፡፡ ስለዚህም በእግዚአብሔር መልአክእየተመሩ ባልታወቁ መንገዶች መሔድነበረባቸው፡፡ ለበርካታ ቀናትና ሳምንታትሸለቆዎችን በመውረድና ኮረብታዎችንእየወጡ ጉዛአቸውን ቀጠሉ፡፡ ሽማግሌውአናጢ ዮሴፍ ከፊት ሁኖ አህያዋንባልተስተካከለውና ማለቂያ የሌለውበሚመስለው የበረሃ መንገድ ላይ ይመራነበር። ሰሎሜም ስንቃቸውን ይዛ ከኋላትከተል ነበር፡፡ በጣም አስቸጋሪ እናአስጨናቂ ጉዞ ነበር፡፡ ቀን ቀንየሚያቃጥለውን የፀሐይ ሐሩር ሌሊትሌሊት ደግሞ የበረሀውን ውርጭ /ብርድ/መታገል ነበረባቸው ምግባቸውንምበተአምራት ያገኙ ነበር፡፡

    በመጨረሻም በመጽሐፈ ስንክሳርእንደተመዘገበው ግንቦት 24 ቀን ግብጽደረሱ፡፡ በግብጽም ባሉ የተለያዩ ከተሞችተዘዋወሩ፣ ጌታም በተለያዩ ቦታዎች በርካታተአምራትን አደረገ፡፡ አንዳንድ ሰዎችተቀብለው ሲያስተናግዷቸው ሌሎች ደግሞአሳድደዋቸዋል፤ መከራንምአጽንተውባቸዋል፡፡ በዚሁ ስደታቸው ወቅትጌታ እና እመቤታችን ወደ ኢትዮጵያምመጥተው ሀገራችንን ባርከዋል።

    ለሦስት ዓመት ተኩል ያህል በስደት ከቆዩበኋላ ሄሮድስ ሞተ። ሄሮድስም ከሞተ በኋላእነሆ የጌታ መልአክ በግብጽ ለዮሴፍበሕልም ታይቶ «የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉትሞተዋልና ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህወደ እስራኤል ሀገር ሂድ አለው፡፡ እርሱምተነስቶ ሕጻኑንና እናቱን ይዞ ወደ እስራኤልሀገር ገባ» ማቴ 2-19-21/፡፡

    ቅዱስ ዮሴፍ ይህንን «.. ወደእስራኤል ሀገር ሂድ..» የሚለውንየመልአኩን ቃል የሰማው ቁስቋምበምትባል በግብጽ ባለች ቦታ ነው፡፡በኋላበዚህች ቦታ ላይ ቤተክርስቲያን በእመቤታችን ስም ተሰርቶ ቅዳሴ ቤቱኅዳር 6 ቀን  ተከብሯል። ሃያ ሦስተኛውየእስክንድርያ ፓትርያርክ ቴዎፍሎስ /384-412 ዓ.ም/ ደግሞ በጌታ እናበእመቤታችን ስደት ወቅት የሆነውን ነገርእንዲገለጥለት ለብዙ ጊዜ ጸሎት ካደረገበኋላ ህዳር 6 ቀን እመቤታችን ተገልጣለትበጉዞው ወቅት የሆነውን ነገር ሁሉነግራዋለች፡፡ ስለዚህ ኅዳር 6 ቀን በሁሉምምሥራቃውያን አብያተ ክርስቲያናትየእመቤታችን ከስደት የመመለሷ ነገርየሚታሰብበት ሁኗል ፡፡

    ነቢያት ስለጌታ ትንቢት በመናገራቸው፣እመቤታችን የጌታ እናት በመሆኗ፣ሐዋርያት ስለጌታ በማስተማራቸው ተሰደዋል፡፡የጌታ አገልጋይም እናትምየሆነችው የእመቤታችን ስደት ግን. . .ከሁሉ የሚለይ ነው፡፡ የጌታችን የኢየሱስክርስቶስና የእመቤታችን የቅድስት ድንግልማርያምን ስደት ልዩ የሚያደርገው: - 
    1.   ሕግን በመተላለፉ ከገነት ተሰዶየነበረውን አዳምን ለመካስ የተደረገበመሆኑ 2.   በግብጽ ነግሦ የነበረውንአምልኮት ጣኦት ለማሳደድ የተደረገ ስለሆነየጌታችንና የእናቱ ስደት ልዩ ነው፡፡

    እመቤታችን ቅድስት ድንግልማርያም ከናዝሬት ወደ ግብጽ ስትሰደድየቀን ሐሩር የሌሊት ቁር አግኝቷታል፡፡ እሾህእየወጋት እንቅፋት እየመታት ተጉዛለች /ተሰዳለች/፤ በስደቷም ረሃብና ጥም፣ችግርና መከራ ደርሶባታል፡፡ በበረሃውወንበዴዎችን ባየች ጊዜም በስደትከሄሮድስ ጭካኔ ከሀገር ያወጣሁትን ልጄንይገድልብኛል ብላ መሪር እንባ አልቅሳለች፡፡በስደቷ ወቅት በደረሰባት ረሐብና ጥምየተነሣ ወደ መንደር ገብታ ብትለምንበችግር ምክንያት የሰው ፊት ማየት ከእሳትየበለጠ ወላፈኑ ስለሚያቃጥል የሰው ፊትገርፏታል፡፡ የትእማን ቤተሰቦችዘብተውባታል፡፡

    «ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ ወደ ዓለም የመጣው ሸክማችንንሊሸከም ነውና ውኃውን ለፍጥረታትየሚሰጥ እርሱ እየጠማው፤ እንስሳትንየሚመግብ እየራበው ምድርን በልምላሜየሚያለብስ ተራቁቶ ፣የኛን ከገነት መሰደድየመጣብንን ዕዳ ሊክስልን ከእናቱ ጋርተሰደደ፤ ድንግል ማርያምም የአምላክ እናትሆና መከራን ቀመሰች፡፡ ጌታን አዝላ በረሐብአለንጋ ተገረፈች፡፡

            በመጨረሻ ግን ያ ሁሉ የመከራናየስቃይ ስደት ሲያበቃ «አንቺ ሱላማጢስሆይ ተመለሽ» ሲል በመኃልየ ማኀልይዘሰሎሞን ተነግሮ የነበረው ትንቢት ይፈጸምዘንድ ከዚያ ሁሉ መከራና ስደት በኋላ ልጇንይዛ ወደ ናዝሬት ተመልሳለች፡፡

            የእመቤታችንን ስደት ስናስብ«ሲነቅፏችሁና ሲያሳድዷችሁ በእኔምምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸትሲነግሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ፡፡ ዋጋችሁበሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁሐሴትም አድርጉ፡፡ ከእናንተም በፊትየነበሩትን ነብያት እንዲሁአሳድደዋቸዋልና» /ማቴ 5-11/ የሚለውንየስደት ዋጋ ጭምር እያሰብን መሆንይገባል፡፡

    ይህንንም የእመቤታችንን ስደት የኢትዮጵያኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6 ድረስበማኅሌትና በመዝሙር ትዘክራለች፡፡ካህናቱም በዕለተ ሰንበት ከምሽት ጀምረውበማኅሌትና በመዝሙር ምስለ ፍቁርወልዳን /የልጇ እና የእርሷ/ ሥዕል ይዘውቤተክርስቲያኑን ይዞራሉ፡፡
    ይህም የእመቤታችንን ስደት ለማጠየቅነው፡፡ ሌሎችም እመቤታችን ቅድስትድንግል ማርያምና ጌታችን መድኃኒታችንኢየሱስ ክርስቶስ የደረሰባቸውን መከራለማስታወስ የፍቃድ ጾም ይጾማሉ፡፡
    እኛ ክርስቲያኖች በቅድስት ቤተክርስቲያንተገኝተን በመንፈስ የሩቁን አቅርበንየእመቤታችንን ስደት በእምነት እያየንበማኅሌተ ጽጌ ድርሰታችን በዜማ«መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ንጹሕ፣ፀአዳ ፣ቀይህና ብሩህ የሚሆን ልጅሽንታቅፈሽ ርኅሩኅ የሆነ ቅዱስ ሚካኤልናቅዱስ ገብርኤልን አስከትለሽ ከሐዘናችንናከችግራችን ታረጋጊን ዘንድ ፈጥነሽድረሽልን» ልንላት ያስፈልጋል፡፡

    በቅዳሴያችንም «ድንግል ሆይ ርጉም በሆነሄሮድስ ዘመን ከልጅሽ ጋር ከሀገር ሀገርስትሸሺ ከአንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ፤ድንግል ሆይ ከዓይንሸ የፈሰሰውንናበተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባአሳስቢ፡፡ ድንግል ሆይ ረሐቡንና ጥሙን፣ችግሩንና ሐዘኑን፣ ከእርሱ ጋርየደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ አሳስቢእንላለን፡፡

    «ድንግል ሆይ ርጉም በሆነ ሄሮድስ ዘመን ከልጅሽ ጋር ከሀገር ሀገር ስትሸሺ ከአንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ
    ድንግል ሆይ ከዓይንሸ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ ፤ 
    ድንግል ሆይ ረሐቡንና ጥሙን፣ ችግሩንና ሐዘኑን፣ ከእርሱ ጋር የደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ አሳስቢ››

    ቅዳሴ ማርያም

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: ዘመነ ጽጌ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top