• በቅርብ የተጻፉ

    Monday 16 November 2015

    ጾመ ሐዋርያት


    በዲ/ን ኅብረት የሺጥላ

    እንኳን ለጾመ ሐዋርያት በሠላም አደረሳችሁ። 

    በየአመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ)የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡ እነዚህአጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸው እሁድ ሲሆንየሚገቡት ደግሞ ሰኞ ቀን ነው፡፡ በየትኛውም አመትይህን ዕለት አይለቁም፡፡

    ስለዚህ የ2004 ጾም ሐዋርያት ግንቦት 27የፊታችን ሰኞ ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥበማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊናሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትንኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮውበበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡

    የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመውየትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩንመረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙእንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውንያህል እጽፍ ዘንድ ብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝአምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋናይድረሰው! አሜን!

    ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾምእንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመንማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታትበፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህምየመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክበርካታ ምስክሮች አሉ፡፡ ስለዚህ ጾሙን እንደእንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለትያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመንአመጣሽ አድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡

          ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸውለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸውካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችንበኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾምመሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡

      ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌበመመሰል ሰፊ ትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደእርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙትስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎችሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገርግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራትይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስአዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱንይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀአቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁምይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱንየወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱምይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)

    በመቀጠልእስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይየሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ ታሪኩን ማንበብወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍልማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡

          በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣልበዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለ ጾመሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህአምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደበኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ››በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገበኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያትከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያትነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡

          ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናትያህል ዘግይቶ እንጂ ወዲያው አይጀምርም፡፡ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያየሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል፡፡ ይህምበጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂየፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸውበመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾምእንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያትየተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋመንፈስ ቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡

          ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስትምህርት ውስጥ ስለ ጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስትዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹበምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊመልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራእንመለከታቸዋለን፡፡

          1ኛ. ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለውየመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉትእንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስየሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራውመውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድናበኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለትነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞ መርዓት (ሴትሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ ዮሐ3.29)

    ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑይችላሉን?›› ሲል ሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰትሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውምእንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂበሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾምተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግንከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩያስረዳል፡፡

    በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘንተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋአይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣትይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘንተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙየመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ ከጸጸትናከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)

    2ኛ. ‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱምየባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይምመጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም)ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥእንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱንማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌውስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡

    በምሳሌው መሠረት በጣፊ ወይም በልብስ ሰፊየተመሰለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በአዲስ እራፊጨርቅ ምሳሌነት የተወከለው ደግሞ ኢየሱስክርስቶስ በአዲስ ኪዳን እንድንጾመው የሠራልንጾም ነው፡፡ የተቀደደውና መጣፊያ የሚያስፈልገውልብስ ደግሞ የሐዋርያት ሕይወት ምሳሌ ነው፡፡

    እንደ ምሳሌው ሁሉ ሰዎች የክርስቶስ ልብሶችይባላሉ፡፡ ‹‹አልባሲሁሰ ለክርስቶስ መሃይምናንእሙንቱ›› እንዲል፡፡ ይህም ‹‹የክርስቶስ ልብሶቹምእመናን ናቸው፡፡›› ማለት ነው፡፡ ክርስቶስምለሰዎች ልብሳቸው ነው፡፡ ሐዋርያው ‹‹እናንተየተጠመቃችሁ ክርስቶስን ለብሳችኋል›› ብሏልና፡፡(ገላ3.27) ምእመናን የክርስቶስ ልብሶች ናቸውማለት የክብሩ መገለጫዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ልብስ የክብር መገለጫ ይሆናልና፡፡ እርሱ ደግሞለምእመናን ልብስ ነው ማለት ጌጣቸው፣ነውራቸውን የሚሸፍንላቸውና ክብራቸውም እርሱነው ማለት ነው፡፡

    ጾም ‹‹እራፊ›› መባሏ ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውምእራፊ የተለያየውን እንደሚያቀራርብና አንድእንደሚያደርግ ጾምም የተለያዩ ፈቃዳት ያሏቸውንነፍስና ሥጋ አንድ ታደርጋለች፡፡ ከዚህም በላይከእግዚአብሔር የተለየውን ሰውም አስታርቃ አንድታደርገዋለች፤ ከመንጋውም እንዲቀላቀልትረዳዋለች፡፡

    ‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱምየባሰ ይሆናል፡፡›› ማለት አንድ የስፌት ባለሙያ ባረጀልብስ ላይ አዲስ እራፊ እንደማይጥፍ ሁሉ ኢየሱስክርስቶስም የሐዋርያት ሰውነት በኃጢአት ያረጀ ሆኖሳለ በመንፈስ ቅዱስ ሳያድስላቸው አዲስ የሠራውንየአዲስ ኪዳን ጾም ጹሙ ብሎ ሐዋርያትንአያዛቸውም ማለት ነው፡፡ ሰውነታቸው ሲታደስ ያንጊዜ ግን ይጾማሉ፡፡     

    ይህ አገላለጥ እግዚአብሔር መንጋዎቹን ያለአቅማቸው እንዲሸከሙ የማያደርግ አዛኝ ጌታመሆኑን ያሳያል፡፡ እንዴት ቢባል ሐዋርያትንሊፈጽሙት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እያሉእንዲጾሙ አላዘዛቸውምና፡፡ ፈጣሪ ለሕዝቡ መቼሕግ መስጠት እንዳለበት በሚገባ ያውቃል፡፡ለእስራኤላውያን በባርነት ሳሉ ዐሥርቱ ትእዛዛትንያልሰጣቸው ስለዚህ ነው፡፡ ቢሰጣቸውምሊጠብቁት አይችሉም ነበርና፡፡ በባርነት ያለ ሰውየራሱ ነጻነት እስከሌለው ድረስ የፈቀደውን ማድረግአይችልም፡፡ በታላላቅ ተአምራት ከባርነትካወጣቸው በኋላ ግን ሕጉን ሰጣቸው፡፡ ስለዚህከክርስቲያን ወገን ማንም ቢሆን ከአቅሙ በላይየሆነ ነገር ፈጣሪ እንዳዘዘው አያስብ፡፡ የታዘዝነውሁሉ በዐቅማችን ልክ እንደሆነ እንመን፡፡

    3ኛ. ‹‹በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖርየለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል: የወይንጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡›› ይህስለ ጾመ ሐዋርያት የተመሰለው ሦስተኛውናየመጨረሻው ምሳሌ ነው፡፡

    በአረጀ አቁማዳ የተመሰለው ሐዋርያት በጸጋመንፈስ ቅዱስ ሳይታደሱ በፊት የነበራቸው ሕይወትሲሆን፤ በአዲስ ወይን የተመሰለው ደግሞ ጌታችንበወንጌል የመሠረተልን ጾም ነው፡፡ የጾም ሕግንየሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ደግሞ በጠጅ ጣዩ(በጠማቂው) ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አዲስ ጠጅ ባረጀአቁማዳ እንደማይጣል አምላካችንም ባልታደሰሕይወታቸው ሐዋርያትን እንዲጾሙ አላዘዛቸውም፡፡

    ቀደም ሲል ጾም ሥጋን ለጊዜው ደስ ባለማሰኘቱበኀዘን እንደሚመሰል ተመልክተን ነበር፡፡ አሁንደግሞ በዚህ ምሳሌ ጾም ነፍስን ደስ የሚያሰኝበመሆኑ በወይን ተመስሎ አገኘነው፡፡ ‹‹ወይንየሰውን ልብ ደስ ያሰኛል›› እንዲል፡፡ (መዝ103.15)

    ጠጅ ጣዮች ሲጥሉ (ሲጠምቁ) ተመልክታችሁታውቃላችሁ? አስቀድመው ቦታ ያዘጋጁለታል፡፡እግር እንዳይበዛበትም ጥላ እንዳይወድቅበትምይጠነቀቃሉ፡፡ እንዳይነፍስበትም ቀን ከሌሊትይተጉለታል፡፡ በመጨረሻ ሥራው አልቆ ሳለ ጠጁከደረቀ (ከጠነከረ) ይላላ ብለው ማር ያልሱታል(ይበርዙታል)፡፡ ከላላ ደግሞ ይድረቅ ብለው ጊዜይሰጡታል፡፡

    በጠጅ ለተመሰለ ለጾምም በዓይነቱ ተመሳሳይከጥቅሙ አኳያ ደግሞ የበለጠ ጥንቃቄ ሊደረግለትያስፈልጋል፡፡ ለጠጅ ቦታ እንደሚዘጋጅለት ለጾምምሰውነትን ማዘጋጀትና ጊዜና ዕለት ወስኖ መመደብበአጠቃላይ ጾምን ማወጅ ይገባል፡፡ ስንዱ እመቤትቤተ ክርስቲያናችን የአጽዋማት ዐዋጅ ስላላት እኛየኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የዚህ ችግርየለብንም፡፡ ለጠጅ እግር እንዳይበዛበትና ጥላእንዳይድቅበት እንደሚጠነቀቁለት ጾማችንምበከንቱ ውዳሴ አጋንንት እንዳይገቡበትና ያለመልካም ሥራ በጾም ብቻ ቀርተን ዋጋውእንዳያንስብን እየተጠነቀቅን መጾም ይገባናል፡፡ጠጅ ደረቀ ይላላ፤ ላላ ይድረቅ እንደሚባል ጾማችንበሕግ ከተሠራልን በላይ ሰዓቱ እንዳይበዛናከዓቅማችን በላይ አልፎ ሰውነታችን እንዳይጎዳ፤እንደዚሁም የአጽዋማትን ሰዓት ሳንጠብቅ ቀርተንምመንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይላላ ማዕከላዊውንስፍራ ይዘን በሕገ ቤተ ክርስቲያን መሠረትበጥንቃቄ መጾም እንደሚገባን ይህ ሦስተኛውምሳሌ ያስረዳናል፡፡

    ይህን ትምህርት ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስክርስቶስ የሚቋጨው ‹‹አዲሱን የወይን ጠጅበአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡››በሚለው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ዐረፍተ ነገሩ አዲስየወይን ጠጅ መጣል ያለበት በአዲስ አቁማዳመሆኑን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ሕይወታቸውበጸጋ መንፈስ ቅዱስ ከታደሰ በኋላ በአዲሱአቁማዳቸው አዲሱን ወይን ጣሉ፡፡ ማለትምበአዲስ ሕይወት የአዲስ ኪዳንን ጾም (ጾመሐዋርያትን) መጾም ጀመሩ፡፡

    አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ሲጣልያፈነዳዋል፡፡ በአዲስ አቁማዳ ሲጣል ግን ያለፋዋልእንጂ ሊያፈነዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ወይኑምአቁማዳውም አዲስ የሆኑ እንደሆነ አቁማዳውወይኑን ያፈላዋል፡፡ ወይኑ ደግሞ አቁማዳውንያለፋዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹ሁለቱም ይጠባበቃሉ››የሚለው ቃል ይፈጸማል፡፡

    ጾምና ሰውነት እንደ ወይንና አቁማዳ ናቸው፡፡ወይንና አቁማዳ እንደሚጠባበቁ(እንደሚጠቃቀሙ) ጾምና ሰውነትም እንዲሁናቸው፡፡ ሰው የጾም ሕግን ቢጠብቅ ሕግም እርሱንትጠብቀዋለች፡፡ ‹‹ይጠባበቃሉ›› የተባለው ለዚህነው፡፡ ይህን የሚያስረዳ ‹‹አኮ ንሕነ ዘነዓቅቦሙለሕገጋት አላ እማንቱ ሕገጋት የዓቅቡነ ለዓቂብወለተፀውኖ›› የሚል ቃል ይገኛል፡፡ ይህም‹‹ሕጎችን እኛ አንጠብቃቸውም፡፡ እነርሱ መጠበቅንይጠብቁናል፤ መጠጊያም ይሆኑናል እንጂ፡፡›› እንደማለት ነው፡፡

    ወይኑ ቆዳውን ማልፋቱ መልካም ነገር ነው፡፡ የለፋቆዳ ብዙ አገልግሎት ስላለው ይፈለጋልና፡፡ ለቀበቶ፣ለቦርሳ፣ ለጫማና ለልብስ የሚሆነው የለፋ ቆዳነው፡፡ የጾምም ጥቅም እዚህ ላይ ነው፡፡ ለልዩ ልዩአገልግሎትና ጥቅም የሚውል መንፈሳዊ ሕይወትእንዲኖረን ከፈለግን በጾም የለፋ (የደከመ) ሰውነትያስፈልገናል፡፡ ቆዳን ማልፋት ማዘጋጀት እንጂከጥቅም ውጭ ማድረግ አይደለም፡፡ ሰውነትንበጾም ማድከምም ለመንፈሳዊ ሥራ ማዘጋጀትእንጂ እንዳይሠራ ማድረግ እንዳልሆነ መረዳትያስፈልጋል፡፡ የታረሰ መሬት ለዘር እንደሚመችበጾም የደከመ ሰውነትም ለመንፈሳዊ ጉዞይመቻል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ››ያለው ለዚህ ነው፡፡ (መዝ108.24)

    ይህን የመሰለ ምሥጢር ያለውን ጾም‹‹የሽማግሌዎች ጾም፣ ከጥንት ያልነበረ›› እያሉበመጽሐፍ እና በቀኖና የሌላ ስም በመስጠትምእመናን እንዳይጾሙት ማድረግ የዲያብሎስትጥቅ የማስፈታት ዘዴ እንጂ ሌላ ምን ሊሆንይችላል?

    ላለመጾም ምክንያት ከመፍጠር ምክንያት ፈጥሮመጾም በእጅጉ ይጠቅማል፡፡ ደሀው ድኅነት ራሱጾም ነው ካለ፤ ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ራሱጾም ነው ካለ ለመጾም ክርስቲያን መሆን ሳይሆንሀገር ወይም ዜግነት መቀየር ሊያስፈልግ ነውማለት ነው? ምእመናን ‹‹ይህ የሽማግሌዎች ጾምነው›› ካሉ ስለ ጾም ማስተማርና ጾመው ማሳየትየሚጠበቅባቸው ‹‹ሰባክያን›› ደግሞ ‹‹ቃለእግዚአብሔር ይመትር ነደ እሳት›› እያሉ ጾም  ሽሮለመብላት ጥቅስ ከጠቀሱ ጾምን በጽሑፍ እንጂበሥራ ላናውቃት ነው ማለት ነው፡፡

    ሐዋርያት እንደታዘዙት ዓለምን ሁሉ ለማስተማርከመሰማራታቸው በፊት መጀመሪያ ያደረጉት ጾምንነው፡፡ ሐዋርያት አልጾሙም ማለት ከላይየተብራራው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢትና ምሳሌሐሰት ሆነ ማለት ነው፡፡ ሎቱ ስብሐት! ቃሉምተፈጽሟል ሐዋርያትም ጾመዋል፡፡ እኛም ጾሙንጾመን የምናስበውና የምንሠራው በጎ ሥራ ሁሉይከናወንልን ዘንድ ፈጣሪ በረድኤት አይለየን!

    "መልካም ጾም ይሁንልን።"

    ወስብሐትለእግዚአብሔር!

    Source: Mekrez blog

    • Blogger Comments
    • Facebook Comments

    1 comments:

    1. የመድኃኒት ንግድ ሥራዬን ለማስፋፋት በተጠቀምኩበት ብድር ለመርዳት ሚስተር ቤንጃሚን ከሚያስፈልጉት በላይ አልፈው ሄዱ ፡፡ Lfdsloans@outlook.com.WhatsApp ... + 19893943740.

      ReplyDelete

    Item Reviewed: ጾመ ሐዋርያት Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top