• በቅርብ የተጻፉ

    Saturday 27 February 2016

    በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እየተደረገ ያለው ድራማዊ መሸላለም፥ “ወይኖ አረሰው ወይኖ ጎረሰው” ዓይነት ነገር ነው /ዜና ቤተ ክርስቲያን/


    የማነ ዘመንፈስ ቅዱስና መሰሎቹ በወርቅ ሐብላትና በወርቅ ብራስሌት ‘ሽልማቶች’ምይበዘብዛሉፐርሰንት አስከፍያለሁ ብሎ በ5 ወራት ብቻ የእጅ ሰዓት፣ የወርቅ ሐብላትና ብራስሌት ሰብስቧልከየአጥቢያው በኃይልና በግድ ፻ሺሕዎች ለ‘ሽልማት’ እየተሰበሰበ እርስበርሳቸው ይሞጋገሱበታልከንፋስ ስልክ ላፍቶ አጥቢያዎች ብቻከብር 300ሺሕ በላይ ተሰብስቦ ወርቃወርቅ ተሸላልመዋልራስን ለማጋነኛ እና ቦታ ለማግኛ የሚካሔዱ መደለያዎች ናቸው፤ ችግሩ በመሸላለም አይፈታም

    /ታዛቢ የክፍላተ ከተማ ሓላፊዎች እና ሠራተኞች/

    *           *          *

    ከምስክር ወረቀት ባለፈ ወርቃወርቅ እና ቁሳቁስ መሸላለሙ ወደ ሙስና ሊመራ ይችላልበድርቅ ለተጐዱት ርዳታ በማሰባሰብ ላይ እያለን በየምክንያቱ መሸላለም ከትዝብት ይጥላልገባእተ ነግሁ ብዙ ሠርተው ቤተ ክርስቲያንን ለገባኡተ ሠርኩ ያስረከቧት ያለመሸላለም ነው“የሚገባችኹን ሠርታችኹ የሚገባንን እንጂ ከሚገባን በላይ አልሠራንም በሉ”ተብለን ታዘናል

    /ዜና ቤተ ክርስቲያን፤ ጥር እና የካቲት ፳፻፰ ዓ.ም./

    *           *          *

    (ርእሰ አንቀጽ)

    መሸላለሙ ወደ ሙስና እንዳያመራ

    … ዜና ቤተ ክርስቲያን ለሀገረ ስብከቱ የሚያሳስበው ዐቢይ ጉዳይ ቢኖር፣ ሀገረ ስብከቱ መኪናዎችን ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት የድካማቸውን ዋጋ በማሰብ በጉዳይ አስፈጻሚነት የመደባቸውን የራሱን ሠራተኞች እንደ ውጭ ሠራተኞች እንደ ውጭ ስፖንሰሮች ሊቆጥራቸውና ሊያጋንናቸው አይገባም፡፡ እንዲኹም በሥራ ብልጫ ላሳዩ አካላት የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት መስጠት ሌላውን ለሥራ የሚያነሣሣ ቢኾንም ለተሸላሚውም ኾነ ለሸላሚው አካል ከምስክር ወረቀት ባለፈ ወርቃወርቅና ሌላም የቁሳቁስ ሽልማት መሸለሙ ወደ ሙስና ሊመራ ይችላል፡፡ መንግሥት የሚሸልመው አምራችና አትራፊ አካላትን እንጂ አክሳሪ አካላትን አይደለም፡፡

    በተለይ በክፍላተ ከተሞች የተደረገውን መሸላለም በተመለከተ መጽሐፍ “ይወድስከ አፈ ነኪር”ማለትም የሌላው አፍ ያመስግንኽ፤ ይላል፡፡አመስጋኞችም እነርሱ፣ ተመስጋኞችም እነርሱ፤ ሽልማቱ የተዘጋጀው በእነርሱ፣ ተሸላሚዎችም እነርሱ፣ “ወይኖ አረሰው ወይኖ ጎረሰው” ዓይነት ነገር ነው፡፡ ወይም ማታ ማታ በቴሌቭዥን ከምናያቸው ድራማዎች ሌላው አዲስ ድራማ ነው፡፡“ሙስና እየተዳከመ ሔዷል” ተብሎ በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ የተነገረውንም ዐረፍተ ነገር ፈጽሞ ይሽረዋልና በዚኽ ጉዳይ ላይ ወደፊት ሀገረ ስብከቱ አጥብቆ ሊያስብበትና ለሽልማቱ ገደብ ሊያበጅለት ይገባዋል፡፡

    በአኹኑ ጊዜ በሀገራችን በተከሠተው የድርቅ አደጋ ምክንያት በአንድ በኩል በድርቅ ለተጐዱ ወገኖቻችን ርዳታ በማሰባሰብ ላይ እያለን በሌላ በኩል በየምክንያቱ ስንሸላለም መታየቱ ቤተ ክርስቲያንን ከትዝብት ላይ የሚጥል እንዳይኾን ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ ገባእተ ነግሁ ብዙ ሥራ ሠርተው ያለፉትና ቤተ ክርስቲያንን ለገባኡተ ሠርኩያስረከቧት ያለአንዳች መሸላለም ነውና፡፡ ጌታችንም“የሚገባችኹን ሠርታችኹ የሚገባንን እንጂ ከሚገባን በላይ አልሠራንም በሉ” በማለት በቅዱስ ወንጌል አዞናልና፡፡

    (ምንጭ፡- ዜና ቤተ ክርስቲያን፤ ርእሰ አንቀጽ፤ ጥር እና የካቲት ፳፻፰ ዓ.ም.

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እየተደረገ ያለው ድራማዊ መሸላለም፥ “ወይኖ አረሰው ወይኖ ጎረሰው” ዓይነት ነገር ነው /ዜና ቤተ ክርስቲያን/ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top