• በቅርብ የተጻፉ

    Thursday 3 December 2015

    ክርስትናና ወጣትነት/ክፍል አንድ/

    በቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅን

      ሰላሌ ሃገረ ስብከት እያለሁ ነዉ።አስታውሳለሁ። ወረዳ ላይ ለአገልግሎት ስወጣየሚያጥመኝ የሚገርምኝም ነገር ነበር።የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችን ሳስተምር ከመካከላቸው ሁል ጊዜ አንድ አዛውንት አያለሁ። ወጣ ካለ ቦታ ከገጠር ነው የሚመጡት። ብርቱ የሆነ መንፈሳዊ ስሜት አላቸው። በአካባቢያቸው ብዙ ጨሌአቃጥለዋል። በዛ ያሉ ምዕመናንም ለንሰሓ አብቅተዋል። ለገጠሩ ሕብረተሰብ ጥሩ አርበኛናቸው። እኒህ አረጋዊ ጉባኤ ሲያበቃ ይጠራቀሙትንአንድ መድበል ጥያቄ ይዘው ይመጣሉ።ከዚያ በቃመጽሓፍ ቅዱስ እየገለጡ መጠየቅ ነው።መናፍቃንንአጥብቀው ስለሚቃወሙ ለእነርሱ የሚሆን መልስበጉንጫቸው አለ።                

              ታድያብዙጊዜየሚናገሩትነገርነበር።እንደውእድሜንወደኋላመመለስአይቻልምእንጂምነውበተቻለናበመለስኩት፣ በእኛጊዜየሃይማኖትትምህርትእንዲህስላልተስፋፋባተሌሆነንነውየኖርነውይላሉ።እናንተታድላችኋልዕድሜያችሁንእየተጠቀማችሁበትነውበማለትበቁጭትይናገራሉ።መዝሙርሲዘመር፣ስብከትሲሰበክ፣ሰንበትት/ቤት ድራማሲሰራ በቃ እርሳቸው ከራሳቸው ጋር ይሟገታሉ።እድሜ ከንቱ ሳላውቀው ሄደና በቃ ወጣትነቴአመለጠኝ ማለት የዘወትር ተግባራቸው ነው።

               አንድቀንመከርኳቸውመንፈሳዊቅናትመቅናታቸውመልካምቢሆንምለቀቢፀተስፋእንዳይዳርጋቸውይተዉ።የእርስዎየጥሪዕድሜይሄከሆነስልሳኛአመትዎንምእንደሃያናሰላሳይቆጥርልዎታልይልቅስባልዎትዕድሜእየተጠቀሙይበርቱብዪአጽናናኋቸው።በወጣቱእንቅስቃሴየሚገረሙምዕመናንይህንይላሉ።ምነዉዳግመኛበተፈጠርኩ፣ምነውወጣትነቴንበድጋሚባገኘሁትይላሉ።ግንአይሆንምዕድሜከነጎደነጎደነው።ከመፀፀትአንዷንዲናር/መንግሥተሰማያትን/ዋጋቸውሆናለመቀበልበገቡበትሰአትገብተውታማኝሆነውድራሻቸውንቢወጡመልካምነው።የሦስተኛውም፣የስድስተኛውም፣የዘጠነኛውም፣ሰአትዋጋአንድዲናርነው።

               ዕድሜሳይሰሩበትያለፈባቸውእንዲህእንዲጽናኑእየመከርንወጣትነትበእጃችንያለግንብዙይጠበቅብናል።ዛሬንእንደቀልድባተሌሆነንካሳለፍነውነገመጸጸትእንድሚመጣመዘንጋትየለብንም።ወጣትነታችንጥሎንሳይሄድእያንዳንዱንደቂቃሰከንድእንዳይባክንአድርገንማሳለፍይጠበቅብናል።ዕድሜበላያችንሳይሮጥእኛበእድሜእንሩጥ።ጊዜንእየገደልነውሳይሆንእየተጠቀምንበትእንዲያልፍእናድርግ።ለሌላውንብረታችንከምንሳሳውበላይለዕድሜእንሳሳ።መክሊቱንቀብሮያለትርፍእንደተገኘውሰነፍባሪያየተሰጠንንጊዜሳናተርፍበትባለቤቱእንዳይመጣብንእንጠንቀቅ።

               ለመጸለይዓይኔን፣ለመስገድወገቤን፣ለመፆምአቅሜንየማንልበትዕድሜወጣትነትነው።ከልብከተነሳንበዚህዕድሜበፈጣሪእርዳታብዙመስራትእንችላለን።ለአገልግሎትከአንዱስፍራወደአንዱብንሮጥ፣ገዳማቱንበየሥፍራውዞረንብንሳለም፣አበውንለመርዳትገንዘብብናወጣ፣ብንረዳ፣መንፈሳዊማህበርብንመሰርትሁሉምይቻላል።ጉልበትን።ገንዘብን፣እውቀትን፣ሁሉንምበስራለማዋልየሚመቸውበዚህዕድሜነው።

              የመናፍቃንንተንኮልለመከላከልዘመኑንዋጅተንመልስማዘጋጀትየምንችልበትእድሜወጣትነትነው።በየዋህነትየኮበለለውን ምዕመንወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመመለስ በአፍበመጽሐፍ የምንልበት ሃይማኖታችንን ለመጠበቅሌትና ቀን የምንደክምበት ዕድሜ ወጣትነትነው።በዚህ ዕድሜ ቅዱስ ዮሐንስ ነገረ መለኮትንአርቅቆ አምጥቆ እንደጻፈ / ዮሐ 21-24 /አትናቴዎስ የሃይማኖት ጸሎትን ከሦስት መቶ አስራስምንት ሊቃውንት ጋር በመሆን እንዳረቀቀ አንርሳ።

              ሰማዕትነትቢመጣአንገትንለሰይፍለስለት፣ሰውነትንለሞትለመስጠትየሚታገሱበትዕድሜወጣትነትነው።ስለቤተክርስቲያንሕይወትንእንኳንዋጋአድርጎለመስጠትይህዕድሜይመቻል።ቀዳሜሰማዕትቅዱስእስጢፋኖስየአይሁድንቁጣሳይፈራእውነትንመስክሮበሰማዕትነትያረፈውበእዚህእድሜመሆኑንምአንዘንጋው።ሊቀሰማዕታትቅዱስጊዮርጊስበዐላውያንነገሥታትፊትስለአምላኩመስክሮየገጠመውንመከራሁሉበጽናትየተቀበለውገናበሃያሦስትዓመቱነው።ከቅዱሳትአንስትቅድስትአርሴማንየመሳሰሉእናቶችመከራንስለሃይማኖታቸውየተቀበሉትበዚህእድሜነው።

              ከዚህሁሉአንጻርበወጣትነትየዕድሜክልልያለንቤተክርስቲያንንበጽናትበትጋትማገልገልይጠበቅብናል።ዕድሜያችንለመንፈሳዊነትየሚመችእንደመሆኑእንጠቀምበት።በጉብዝናችንወራትፈጣሪያችንንማሰብእንዳለብንአንዘንጋ።/መጽ መክ12-1/ ውድ የሆነዉን የዕድሜ ክልላችንንለእግዚአብሔር አንንፈገው።ይልቁንም ከእጁየተቀበልነዉን እድሜ ፣ጤና ….መልሰን ለፈጣሪእንስጠው።ጤናችን ፣ጉልበታችን ፣ገንዘባችን ሁሉየእርሱ ነው።የእኛ የሆነ አንዳች ነገርየለንም።ሌላው ቀርቶ እኛም እራሳችን የእርሱነን።ይህንን ሳንረሳ ሁል ጊዜ ለፈጣሪ ታማኝ እንሁን።

             ወደፊትበዚህዓምድወጣቱበቤተክርስቲያንእንዴትመመላለስእንዳለበት፣መንፈሳዊለመሆንምንማድረግእንዳለበትበሰፊውእንመለከታለን።የሚገጥሙትንምፈተናዎችበጊዜዉናበሰዓቱእንዳስሳለን።ለአሁኑይቆየን።

    • የተሰጡ አስተያየቶች
    • በፌስቡክ (Facebook) የተሰጡ አስተያየቶች

    0 comments:

    Post a Comment

    Item Reviewed: ክርስትናና ወጣትነት/ክፍል አንድ/ Rating: 5 Reviewed By: Getahun Amare - ጌታሁን አማረ
    Scroll to Top